Logo
Getu Temesgen
“ ብዙ ግብ ማስቆጠር እንችል ነበር “ አርቴታ

“ አርሰናል ግድለኛ ነበር “ ኦሊቨር ግላስነር
#ethiopia | የመድፈኞቹ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ በሁለት ተከታታይ አመታት ግማሽ ፍፃሜ መድረሳቸውን እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል።

በጨዋታው “ ብዙ የግብ እድሎችን ፈጥረናል “ ያሉት አርቴታ “ ተጨማሪ ግቦች ማስቆጠር እንችል ነበር “ ብለዋል።

“ ግማሽ ፍፃሜ በመድረሳችን በጣም ደስተኛ ነኝ “ ሲሉ አሰልጣኙ ጨምረው ተናግረዋል።

ለነበረው የስታዲየም ድባቡ ደጋፊን ያመሰገኑት አርቴታ “ ለሁላችሁም መልካም በዓል ይሁንላችሁ መልካም አዲስ አመት “ ሲሉ ምኞታቸውን ገልጸዋል።

የክሪስታል ፓላሱ አሰልጣኝ ኦሊቨር ግላስነር በበኩላቸው ግብ ጠባቂው ቤኒቴዝ “ ጨዋታው ላይ እንድንቆይ አድርጎናል “ ሲሉ አወድሰውታል።

አክለውም “ በመለያ ምቱ ወቅት ግን አርሰናል አእድለኛ ነበር “ ሲሉ ገልጸዋል።
#ts #sports #gtmc

7 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.