Logo
Getu Temesgen
“ የአፍሪካ ዋንጫ ከአውሮፓ ዋንጫ አያንስም “ አኪም አብደላህ

“ ሞሮኮን ፈፅሞ አንፈራም “
#ethiopia | የኮሞሮስ ብሔራዊ ቡድን የኋላ መስመር ተሰላፊ አኪም አብደላህ የአፍሪካ ዋንጫ በትልቅ ደረጃ ያለ መሆኑን ተናግሯል።

“ የአፍሪካ ዋንጫ እንደ አውሮፓ ዋንጫ ነው የሚጎድለው ነገር የለውም “ ያለው ተጨዋቹ “ ይህንን ካለፈው አፍሪካ ዋንጫ ማየት እንችላለን “ ብሏል።

አክሎም “ አሁን የአፍሪካ እግርኳስ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ነው የኩራት ምንጭ ሆኗል አለም እያየው እንደሆነ እናውቃለን “ ሲል ገልጿል።

ስለ ምሽቱ የሞሮኮ ጨዋታ ያነሳው ተጨዋቹ “ እነሱም እንደኛው ሰው ናቸው ፤ አንፈራቸውም ምንም የሚያስፈራን ነገር አይኖርም ብሏል።

“ ጥሩ ተጨዋቾች አሏቸው ነገርግን ማናቸውም አያስጉንም ጫናው በእኛ ላይ አይደለም ፤ ጨዋታችንን እንጫወታለን መጨረሻ ላይ የሚሆነውን እናያለን።“አኪም አብደላህ
#ts #sports #gtmc

8 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.