Logo
FastMereja
ታማኝነት‼

ዛሬ ሰኞ አይደል ‎የባቲ ገበያ ድምቅ ውሎ የዋለበት ቀን ነው።በዚህ መሐል አንድ እህታች የቤት አስቤዛ ገዝታ በቀን ሰራተኛ በማሸከም ወደ ቤት ከገበያ እየወጣች እያለ ተጠፋፉ።

ታማኙ የቀን ሰራተኛ እቃውን ይዞ ለፖሊስ አስረክቧል።የባቲ ከተማ አስተዳደር ፖሊስም ወጣቱን አመስግኖ እቃውን ተረክቧል። ባለቤት ነኝ የሚል ይውሰድ ብሏል።

ወዳጄ እንደዚህ አይነቱን ታማኝ ካላመሰገንክ አደራ ጠባቂ ትውልድ ማፍራት አይቻልም።ተባረክልኝ።

Via: Wasu Mohammed - Mereja

7 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.