የዋልያዎቹ ተጫዋች በኦማን ጎል አስቆጥሯል !
#ethiopia | በኦማን ሊግ እየተጫወተ የሚገኘው የዋልያዎቹ የመሐል እና የፊት መስመር ተጫዋች ከንአን ማርክነ የመጀመሪያ ጎሉን ለክለቡ አስቆጥሯል።
ከንአን ቡድኑ አል ሸባብ በትላንትናው ዕለት በ ጄቱር ካፕ ኢብሪ ክለብን 4ለ0 ባሸነፈበት ጨዋታ ለቡድኑ አንድ ጎል ማስቆጠር ችሏል።
ከንአን ማርክነ ቡድኑ ከተቀላቀለ በኃላ ባደረጋቸው ያለፉት ሶስት ጨዋታዎች በቋሚነት ተሰልፎ መጫወት ችሏል።
#ts #sport #gtmc