11 days ago
መድፈኞቹ የክብር ዋንጫቸውን ዛሬ ያነሳሉ፤ ሻምፒዮኑ አርሰናል ወደ ክሪስታል ፓላስ ሜዳ ያቀናል
***********************
መድፈኞቹ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን በበላይነት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ፣ የድል ምልክት የሆነውን የሊጉን ባለወርቅ ዋንጫ ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ይረከባሉ።
አርሰናል የሊጉን ዋንጫ አስቀድሞ ማረጋገጥ ቢችልም፣ የስኬቱ መሀንዲስ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ትኩረት ግን አሁንም ጨዋታው ላይ ብቻ በመሆኑ ቡድኑ ዛሬ ወደ ሴልኸርስት ፓርክ አቅንቶ ከክሪስታል ፓላስ ጋር ምሽት 12:00 ሰዓት ላይ ፍልሚያውን ያደርጋል።
ተጫዋቾቹን በስታዲየም በአካል ለማየት በጉጉት ለሚጠብቁ ደጋፊዎች ዛሬ ሜዳው በደስታ ማዕበል እንደሚሞላ ይጠበቃል።
የቡድኑ የልብ ትርታ የሆነው ጠንካራው ተከላካይ ዊሊያም ሳሊባ ስለ አስደናቂው ስኬት ሲናገር፣ ከመጋቢት ወር ጀምሮ እንደሚያሸንፉ ይሰማው እንደነበርና በተለይም ከኤቨርተን ጨዋታ በኋላ ነገሩ ፍንትው ብሎ እንደታየው ገልጿል።
ሳሊባ አክሎም “አሁን እኛ ሻምፒዮኖች ነን፤ ቀጣዩ ኢላማችን ደግሞ ፒኤስጂን አሸንፈን ታሪክ መስራት ነው” በማለት ቡድኑ ለአውሮፓ መድረክ ያለውን ከፍተኛ መነሳሳትና መተማመን ለደጋፊዎቹ አብስሯል።
የመድፈኞቹ ስኬት ከተቀናቃኞቻቸው ዘንድም ትልቅ አድናቆትን እያስገኘ ይገኛል። የሊቨርፑሉ አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ለአርሰናል ያላቸውን ክብር ሲገልጹ፣ በእንግሊዝ ሊግ ማሸነፍ እጅግ ከባድ መሆኑን ጠቅሰው አርሰናል ድንቅ ስራ መሥራቱን መስክረዋል።
#arsenal #champions #premierleague #arteta #saliba #coyg
***********************
መድፈኞቹ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን በበላይነት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ፣ የድል ምልክት የሆነውን የሊጉን ባለወርቅ ዋንጫ ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ይረከባሉ።
አርሰናል የሊጉን ዋንጫ አስቀድሞ ማረጋገጥ ቢችልም፣ የስኬቱ መሀንዲስ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ትኩረት ግን አሁንም ጨዋታው ላይ ብቻ በመሆኑ ቡድኑ ዛሬ ወደ ሴልኸርስት ፓርክ አቅንቶ ከክሪስታል ፓላስ ጋር ምሽት 12:00 ሰዓት ላይ ፍልሚያውን ያደርጋል።
ተጫዋቾቹን በስታዲየም በአካል ለማየት በጉጉት ለሚጠብቁ ደጋፊዎች ዛሬ ሜዳው በደስታ ማዕበል እንደሚሞላ ይጠበቃል።
የቡድኑ የልብ ትርታ የሆነው ጠንካራው ተከላካይ ዊሊያም ሳሊባ ስለ አስደናቂው ስኬት ሲናገር፣ ከመጋቢት ወር ጀምሮ እንደሚያሸንፉ ይሰማው እንደነበርና በተለይም ከኤቨርተን ጨዋታ በኋላ ነገሩ ፍንትው ብሎ እንደታየው ገልጿል።
ሳሊባ አክሎም “አሁን እኛ ሻምፒዮኖች ነን፤ ቀጣዩ ኢላማችን ደግሞ ፒኤስጂን አሸንፈን ታሪክ መስራት ነው” በማለት ቡድኑ ለአውሮፓ መድረክ ያለውን ከፍተኛ መነሳሳትና መተማመን ለደጋፊዎቹ አብስሯል።
የመድፈኞቹ ስኬት ከተቀናቃኞቻቸው ዘንድም ትልቅ አድናቆትን እያስገኘ ይገኛል። የሊቨርፑሉ አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ለአርሰናል ያላቸውን ክብር ሲገልጹ፣ በእንግሊዝ ሊግ ማሸነፍ እጅግ ከባድ መሆኑን ጠቅሰው አርሰናል ድንቅ ስራ መሥራቱን መስክረዋል።
#arsenal #champions #premierleague #arteta #saliba #coyg