2 months ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በጁባ
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ ለሚያካሂደው ዘመናዊ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ግንባታ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የደቡብ ሱዳን መንግሥት አስታውቋል።
ኮርፖሬሽኑ ግንባታውን ለማከናወን የሚያስችለውን ስምምነት የፈረመ ሲሆን፣ የህንጻ ግንባታ ቦታዎች መረጣ እና ተያያዥ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች አፈጻጸም በግዛቱ የኮንስትራክሽን እና ቤቶች ኮርፖሬሽን በቀረበ የጥናት ሪፖርት አማካኝነት በዝርዝር ተገምግሟል።
ቀደም ሲል በአዲስ አበባ ከተማ የተደረሰውን የመግባቢያ ስምምነት ወደ ተግባር የሚቀይረው ይኸው አዲስ ውል በጁባ ከተማ ተፈርሟል።
ስምምነቱን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና የደቡብ ሱዳን ሴንተራል ኢኳቶሪያል ግዛት አስተዳዳሪ ክቡር ኢማኑኤል አድል ተፈራርመውታል። በዚህም መሠረት ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ ዘመናዊ የንግድና የመኖሪያ ሕንጻዎችን የሚገነባ ይሆናል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል ከደቡብ ሱዳን መንግሥት ልዩ መልዕክተኛ ክብርት አዱት ኪር ጋር ውጤታማ ውይይት አካሂደዋል።
በውይይቱ መድረክ ላይ በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ክቡር ደሊል ከድር እና በደቡብ ሱዳን በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የተሰማሩት ታዋቂው ባለሀብት ዶክተር አይሸሽም ተካ ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ ክብርት አዱት ኪር ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ ለሚያካሂደው የቤት ልማት ፕሮግራም የደቡብ ሱዳን ፌዴራል መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።
ይህ የቤት ግንባታ መጀመር በሁለቱ እህትማማች አገራት መካከል ያለውን ጠንካራና ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ያላቸውን ሙሉ እምነት በመግለጽ፣ የደቡብ ሱዳን መንግሥት ለስምምነቱ ተግባራዊነት ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ዶክተር ረሻድ ከማል በበኩላቸው፣ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን የቤት ልማት ዘርፍ የተሰማራው የጋራ ተጠቃሚነትን፣ አብሮነትን እና ወንድማማችነትን መርህ አድርጎ መሆኑን ገልጸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናቆ ግንባታው በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና በርሳቸው የሚመራው የሥራ ልዑካን ቡድን ለአራት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን ጉብኝት አጠናቆ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል።
#የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ኢትዮጵያ #ደቡብሱዳን #ጁባ #ቤትልማት #ኮንስትራክሽን #ኢንቨስትመንት #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ ለሚያካሂደው ዘመናዊ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ግንባታ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የደቡብ ሱዳን መንግሥት አስታውቋል።
ኮርፖሬሽኑ ግንባታውን ለማከናወን የሚያስችለውን ስምምነት የፈረመ ሲሆን፣ የህንጻ ግንባታ ቦታዎች መረጣ እና ተያያዥ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች አፈጻጸም በግዛቱ የኮንስትራክሽን እና ቤቶች ኮርፖሬሽን በቀረበ የጥናት ሪፖርት አማካኝነት በዝርዝር ተገምግሟል።
ቀደም ሲል በአዲስ አበባ ከተማ የተደረሰውን የመግባቢያ ስምምነት ወደ ተግባር የሚቀይረው ይኸው አዲስ ውል በጁባ ከተማ ተፈርሟል።
ስምምነቱን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና የደቡብ ሱዳን ሴንተራል ኢኳቶሪያል ግዛት አስተዳዳሪ ክቡር ኢማኑኤል አድል ተፈራርመውታል። በዚህም መሠረት ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ ዘመናዊ የንግድና የመኖሪያ ሕንጻዎችን የሚገነባ ይሆናል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል ከደቡብ ሱዳን መንግሥት ልዩ መልዕክተኛ ክብርት አዱት ኪር ጋር ውጤታማ ውይይት አካሂደዋል።
በውይይቱ መድረክ ላይ በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ክቡር ደሊል ከድር እና በደቡብ ሱዳን በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የተሰማሩት ታዋቂው ባለሀብት ዶክተር አይሸሽም ተካ ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ ክብርት አዱት ኪር ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ ለሚያካሂደው የቤት ልማት ፕሮግራም የደቡብ ሱዳን ፌዴራል መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።
ይህ የቤት ግንባታ መጀመር በሁለቱ እህትማማች አገራት መካከል ያለውን ጠንካራና ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ያላቸውን ሙሉ እምነት በመግለጽ፣ የደቡብ ሱዳን መንግሥት ለስምምነቱ ተግባራዊነት ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ዶክተር ረሻድ ከማል በበኩላቸው፣ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን የቤት ልማት ዘርፍ የተሰማራው የጋራ ተጠቃሚነትን፣ አብሮነትን እና ወንድማማችነትን መርህ አድርጎ መሆኑን ገልጸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናቆ ግንባታው በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና በርሳቸው የሚመራው የሥራ ልዑካን ቡድን ለአራት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን ጉብኝት አጠናቆ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል።
#የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ኢትዮጵያ #ደቡብሱዳን #ጁባ #ቤትልማት #ኮንስትራክሽን #ኢንቨስትመንት #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን የቤት ግንባታ ለማከናወን ስምምነት ተፈራረመ
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ በቤት ልማት ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችለውን ታሪካዊ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ይህ ስምምነት የተደረገው በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን መሪዎች መካከል የተደረሰውን የጋራ ልማት ትብብር መነሻ በማድረግ ሲሆን በኮርፖሬሽኑ እና በደቡብ ሱዳን ማዕከላዊ ኢኳቶሪያል ግዛት መካከል የተፈጸመ ነው።
ስምምነቱን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በጁባ ከተማ በጋራ ፈርመዋል።
ውሉ ኮርፖሬሽኑ ያለውን የቴክኒክ ብቃት እና የዳበረ ልምድ ተጠቅሞ በጁባ ዘመናዊ መኖሪያዎችን፣ የንግድ ማዕከላትንና የመንግሥት ቢሮዎችን እንዲገነባ ዕድል ይሰጣል።
ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት ኮርፖሬሽኑ በምሥራቅ አፍሪካና በመላው አህጉሪቱ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቅረብ ባቀደው መሠረት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተሸጋግሯል።
የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በበኩላቸው የኢትዮጵያ የከተሞች ዕድገትና የቤት ልማት ተሞክሮ ለአፍሪካውያን አርአያ መሆኑን ጠቅሰው ይህን ተሞክሮ በጁባ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
ይህ ትብብር የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ትስስር ከማጠናከሩ ባሻገር በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ለመስጠት ያስችላል።
የስምምነቱን አፈጻጸም የሚከታተልና ዝርዝር የፕሮጀክት ሰነዶችን የሚያዘጋጅ የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴ እንዲቋቋምም መግባባት ላይ ተደርሷል።
#ደቡብሱዳን #ቤትልማት #ኮንስትራክሽን #ኢኮኖሚ #አፍሪካ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ በቤት ልማት ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችለውን ታሪካዊ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ይህ ስምምነት የተደረገው በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን መሪዎች መካከል የተደረሰውን የጋራ ልማት ትብብር መነሻ በማድረግ ሲሆን በኮርፖሬሽኑ እና በደቡብ ሱዳን ማዕከላዊ ኢኳቶሪያል ግዛት መካከል የተፈጸመ ነው።
ስምምነቱን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በጁባ ከተማ በጋራ ፈርመዋል።
ውሉ ኮርፖሬሽኑ ያለውን የቴክኒክ ብቃት እና የዳበረ ልምድ ተጠቅሞ በጁባ ዘመናዊ መኖሪያዎችን፣ የንግድ ማዕከላትንና የመንግሥት ቢሮዎችን እንዲገነባ ዕድል ይሰጣል።
ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት ኮርፖሬሽኑ በምሥራቅ አፍሪካና በመላው አህጉሪቱ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቅረብ ባቀደው መሠረት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተሸጋግሯል።
የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በበኩላቸው የኢትዮጵያ የከተሞች ዕድገትና የቤት ልማት ተሞክሮ ለአፍሪካውያን አርአያ መሆኑን ጠቅሰው ይህን ተሞክሮ በጁባ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
ይህ ትብብር የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ትስስር ከማጠናከሩ ባሻገር በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ለመስጠት ያስችላል።
የስምምነቱን አፈጻጸም የሚከታተልና ዝርዝር የፕሮጀክት ሰነዶችን የሚያዘጋጅ የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴ እንዲቋቋምም መግባባት ላይ ተደርሷል።
#ደቡብሱዳን #ቤትልማት #ኮንስትራክሽን #ኢኮኖሚ #አፍሪካ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Comments