8 months ago
#እንኳን_ደሰ_አላችሁ !
#ethiopia | የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ለአህጉር አቀፉ የአፍሪካ የባህል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ኮንፌዴሬሽን (ATSGC) ያቀረበው የአባልነት ጥያቄ ተቀባይነት አገኘ።
የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ለአህጉር አቀፉ የአፍሪካ የባህል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ኮንፌዴሬሽን (African traditional sports and games confederation) ያቀረበው የአባልነት ጥያቄ በዛሬው ዕለት ተቀባይነት አገኝቷል።
በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ህይወት መሀመድ የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ በመግለፅ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አክለውም በሀገራችን በአራቱም አቅጣጫ በኩል የሚገኙ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የውበት፣ የማንነት፣ የኩራት እና የጀግንነት ተምሳሌታዊ መገለጫ የሆኑ ብርቅዬ ባህላዊ ስፖርቶቻችንን በሀገር አቀፍ፤ በአህጉር አቀፍ እና በአለም አቀፍ ደረጃ በስፋት ለማስተዋወቅ ብሎም ተዘውታሪ ለማድረግ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን አመርቂ ውጤቶችን ያስመዘገቡ ከፍተኛ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
አያይዘውም ፌዴሬሽኑ በ2018 ዓ.ም ለመከወን ከያዛቸው እቅዶች መካከል አንዱ የሆነውን በአህጉር አቀፉ የአፍሪካ የባህል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ኮንፌዴሬሽን (African traditional sports and games confederation) አባል የመሆን እቅድ በአጭር ጊዜ ውስጥ በተደረገ ከፍተኛ እንቅስቃሴ በአመቱ የመጀመሪያ ወር ላይ ልናሳካ ችለናል ያሉ ሲሆን በቀጣይ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር ድንበር ተሻጋሪ የሆነ ግንኙነቶችን በመፍጠር ባህላዊ ስፖርቶቻችንን ለማስተዋወቅ እና የባህል ልውውጦችን ለማድረግ ጉልህ ሚናን ይጫወታል ብለዋል።
በተጨማሪም ፌዴሬሽኑ በአሁኑ ወቅት ልዩ የሆነ ትኩረትን በመስጠት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን የ2026 African traditional sports and multi event festival ለማዘጋጀት መጠነ ሠፊ ስራዎችን እየሠራ እንደሚገኝ ወ/ሮ ህይወት ጠቁመዋል።
በመጨረሻም በፌዴሬሽኑ በኩል ለሚሰሩ በርካታ ስራዎች ፈር የቀደደ ታሪካዊ ጅማሮ በመሆኑ ሁላችንም የዚህ ጅማሮ አካል በመሆን ባህላዊ ስፖርቶቻችንን በማሳደግ፣ በማስተዋውቅ፣ በመጠበቅ እና በማልማት ሀላፊነታችን ልንወጣ ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
#ethiopia | የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ለአህጉር አቀፉ የአፍሪካ የባህል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ኮንፌዴሬሽን (ATSGC) ያቀረበው የአባልነት ጥያቄ ተቀባይነት አገኘ።
የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ለአህጉር አቀፉ የአፍሪካ የባህል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ኮንፌዴሬሽን (African traditional sports and games confederation) ያቀረበው የአባልነት ጥያቄ በዛሬው ዕለት ተቀባይነት አገኝቷል።
በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ህይወት መሀመድ የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ በመግለፅ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አክለውም በሀገራችን በአራቱም አቅጣጫ በኩል የሚገኙ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የውበት፣ የማንነት፣ የኩራት እና የጀግንነት ተምሳሌታዊ መገለጫ የሆኑ ብርቅዬ ባህላዊ ስፖርቶቻችንን በሀገር አቀፍ፤ በአህጉር አቀፍ እና በአለም አቀፍ ደረጃ በስፋት ለማስተዋወቅ ብሎም ተዘውታሪ ለማድረግ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን አመርቂ ውጤቶችን ያስመዘገቡ ከፍተኛ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
አያይዘውም ፌዴሬሽኑ በ2018 ዓ.ም ለመከወን ከያዛቸው እቅዶች መካከል አንዱ የሆነውን በአህጉር አቀፉ የአፍሪካ የባህል ስፖርቶች እና ጨዋታዎች ኮንፌዴሬሽን (African traditional sports and games confederation) አባል የመሆን እቅድ በአጭር ጊዜ ውስጥ በተደረገ ከፍተኛ እንቅስቃሴ በአመቱ የመጀመሪያ ወር ላይ ልናሳካ ችለናል ያሉ ሲሆን በቀጣይ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር ድንበር ተሻጋሪ የሆነ ግንኙነቶችን በመፍጠር ባህላዊ ስፖርቶቻችንን ለማስተዋወቅ እና የባህል ልውውጦችን ለማድረግ ጉልህ ሚናን ይጫወታል ብለዋል።
በተጨማሪም ፌዴሬሽኑ በአሁኑ ወቅት ልዩ የሆነ ትኩረትን በመስጠት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን የ2026 African traditional sports and multi event festival ለማዘጋጀት መጠነ ሠፊ ስራዎችን እየሠራ እንደሚገኝ ወ/ሮ ህይወት ጠቁመዋል።
በመጨረሻም በፌዴሬሽኑ በኩል ለሚሰሩ በርካታ ስራዎች ፈር የቀደደ ታሪካዊ ጅማሮ በመሆኑ ሁላችንም የዚህ ጅማሮ አካል በመሆን ባህላዊ ስፖርቶቻችንን በማሳደግ፣ በማስተዋውቅ፣ በመጠበቅ እና በማልማት ሀላፊነታችን ልንወጣ ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
11 months ago
1.69 ትሪሊዮን ብር : አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ
እንኳን ደስ አለን!! እንኳን ደስ አላችሁ!!
#ethiopia | ባጠናቀቅነው በጀት ዓመት ብቻ ከ515 ቢሊየን ብር በላይ ተጨማሪ አዲስ ተቀማጭ ገንዘብ አሰባስበን አጠቃላይ ተቀማጭ 1.69 ትሪሊዮን ብር በማድረስ ታላቅ ስኬት አስመዝግበናል
የተከበራችሁ ደምበኞቻችንና የተወደዳችሁ የባንካችን ሰራተኞች!፤
ሰላምታዬ በያላችሁበት ይድረሳችሁ፤
ባጠናቀቅነው የ2024/25 በጀት ዓመት በፈረንጆቹ ጁን ወር መጨረሻ፤ ባንካችን ከ515 ቢሊየን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ የማሰባሰብ ተግባር በማሳካቱ የተሰማኝን ከፍ ያለ ደስታ ልገልጽላችሁ እወዳለሁ፡፡ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ በባንካችን የተመዘገበ አዲስ ታሪክ ነው፡፡ ለዚሁ ታላቅ ስኬት አሻራችሁን ላኖራችሁ ሁሉ እንኳን ደሰ አላችሁ እላለሁ፡፡
በተለይም ባንካችን ላይ እምነታችሁን አሳድራችሁ አብራችሁን ለሰራችሁ ውድ ደንበኞቻችን ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡ ይህ ስኬት የናንተ እገዛና ያላሰለሰ ጥረት ድምር ውጤት ነው፡፡ የባንካችን የዳይሬክተሮች ቦርድ አመራሮችና አባላት ለውጤቱ መሳካት ያደረጋችሁት ክትትልና ድጋፍ የነበረው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ ነው፡፡ ድካማችሁ ፍሬ አፍርቶ ለማየት ስለበቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ የባንካችን የስራ አመራር አባላት፣ የሪጅን እና የዋናው መ/ቤት ሰራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች፣ የዲስትሪክቶችና የቅርንጫፍ ሰራተኞቻችን፣ የባንካችንን ስትራቴጂዎች እና አቅጣጫዎች ለመተግበር ያሳያችሁት ቁርጠኝነት ለስኬቱ ከፍ ያለ ሚና አበርክቷል፡፡
እዚህ ስኬት ላይ ለመድረስ ያሳየነው ታታሪነት እና ትጋት ፍሬ ሰጥቶን ለማየት በመብቃታችን ስሜቱ ጥልቅ ነው፡፡ በየደረጃው ያሉ የስራ ክፍሎቻችን በትብብርና በትጋት የመስራት ውጤት አስረጅ ነው፡፡ የባንካችን ሰራተኞች በጋራ ሆነን እና ተናበን ያሳየነው ጥረት ውጤት ለመሆኑም ጥርጥር የለውም፡፡
ደንበኞቻችንን ለማገልገል ባሳየነው ቁርጠኝነት የተገኘ የላቀ አፈጻጸም ስለመሆኑም አምናለሁ፡፡ ደንበኞቻችንን በማስቀደም እና ፍላጎታቸውን በመረዳት፤ ተገቢውን አገልግሎት ለማቅረብ ያደረግነው ትጋት ማሳያ ነው፡፡
ለባንካችን ይህ ስኬት ትርጉሙ ከፍ ያለ ነው፡፡ ይህም፡-
የባንካችን ሰራተኞች ታታሪነትና ጠንካራነት ማሳያ
በትብብር የመስራት እና ለአንድ ዓላማ የመቆም ምልክት
ለባንካችን ያለንን ፍቅርና የባለቤትነት ስሜት ምስክር
ለደንበኞቻችን የምንሰጠውን አክብሮትና ዋጋ የገለጽንበት እና
የባንካችንን ራዕይ ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት ያመላከትንበት ነው ማለትም ይቻላል፡፡
በሌላ መልኩም ባንካችን ፈተናዎችን እና ተግዳሮቶችን በመቋቋም፣ በጥንካሬ እና በከፍታ መዝለቅ የቻለ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡
የተከበራችሁ የባንካችን ሰራተኞች!፤
ለዚህ ስኬት አስተዋጽኦ ለነበራችሁ ትጋት ሁሉ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። ያሳየነው ስኬት ድንቅ እና ሁላችንንም የሚያስደምም ነው፡፡ ሁላችንም ልንኮራ ይገባናል። ለመጪው በጀት ዓመት ታላቅ ስንቅ ሆኖን በላቀ ከፍታ ለመጓዝ ጠንክረን እንቀጥል፡፡
ለተሻለ ስኬት እንትጋ!
አመሰግናለሁ፡፡
አቤ ሳኖ
ፕሬዝዳንት
እንኳን ደስ አለን!! እንኳን ደስ አላችሁ!!
#ethiopia | ባጠናቀቅነው በጀት ዓመት ብቻ ከ515 ቢሊየን ብር በላይ ተጨማሪ አዲስ ተቀማጭ ገንዘብ አሰባስበን አጠቃላይ ተቀማጭ 1.69 ትሪሊዮን ብር በማድረስ ታላቅ ስኬት አስመዝግበናል
የተከበራችሁ ደምበኞቻችንና የተወደዳችሁ የባንካችን ሰራተኞች!፤
ሰላምታዬ በያላችሁበት ይድረሳችሁ፤
ባጠናቀቅነው የ2024/25 በጀት ዓመት በፈረንጆቹ ጁን ወር መጨረሻ፤ ባንካችን ከ515 ቢሊየን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ የማሰባሰብ ተግባር በማሳካቱ የተሰማኝን ከፍ ያለ ደስታ ልገልጽላችሁ እወዳለሁ፡፡ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ በባንካችን የተመዘገበ አዲስ ታሪክ ነው፡፡ ለዚሁ ታላቅ ስኬት አሻራችሁን ላኖራችሁ ሁሉ እንኳን ደሰ አላችሁ እላለሁ፡፡
በተለይም ባንካችን ላይ እምነታችሁን አሳድራችሁ አብራችሁን ለሰራችሁ ውድ ደንበኞቻችን ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡ ይህ ስኬት የናንተ እገዛና ያላሰለሰ ጥረት ድምር ውጤት ነው፡፡ የባንካችን የዳይሬክተሮች ቦርድ አመራሮችና አባላት ለውጤቱ መሳካት ያደረጋችሁት ክትትልና ድጋፍ የነበረው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ ነው፡፡ ድካማችሁ ፍሬ አፍርቶ ለማየት ስለበቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ የባንካችን የስራ አመራር አባላት፣ የሪጅን እና የዋናው መ/ቤት ሰራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች፣ የዲስትሪክቶችና የቅርንጫፍ ሰራተኞቻችን፣ የባንካችንን ስትራቴጂዎች እና አቅጣጫዎች ለመተግበር ያሳያችሁት ቁርጠኝነት ለስኬቱ ከፍ ያለ ሚና አበርክቷል፡፡
እዚህ ስኬት ላይ ለመድረስ ያሳየነው ታታሪነት እና ትጋት ፍሬ ሰጥቶን ለማየት በመብቃታችን ስሜቱ ጥልቅ ነው፡፡ በየደረጃው ያሉ የስራ ክፍሎቻችን በትብብርና በትጋት የመስራት ውጤት አስረጅ ነው፡፡ የባንካችን ሰራተኞች በጋራ ሆነን እና ተናበን ያሳየነው ጥረት ውጤት ለመሆኑም ጥርጥር የለውም፡፡
ደንበኞቻችንን ለማገልገል ባሳየነው ቁርጠኝነት የተገኘ የላቀ አፈጻጸም ስለመሆኑም አምናለሁ፡፡ ደንበኞቻችንን በማስቀደም እና ፍላጎታቸውን በመረዳት፤ ተገቢውን አገልግሎት ለማቅረብ ያደረግነው ትጋት ማሳያ ነው፡፡
ለባንካችን ይህ ስኬት ትርጉሙ ከፍ ያለ ነው፡፡ ይህም፡-
የባንካችን ሰራተኞች ታታሪነትና ጠንካራነት ማሳያ
በትብብር የመስራት እና ለአንድ ዓላማ የመቆም ምልክት
ለባንካችን ያለንን ፍቅርና የባለቤትነት ስሜት ምስክር
ለደንበኞቻችን የምንሰጠውን አክብሮትና ዋጋ የገለጽንበት እና
የባንካችንን ራዕይ ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት ያመላከትንበት ነው ማለትም ይቻላል፡፡
በሌላ መልኩም ባንካችን ፈተናዎችን እና ተግዳሮቶችን በመቋቋም፣ በጥንካሬ እና በከፍታ መዝለቅ የቻለ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡
የተከበራችሁ የባንካችን ሰራተኞች!፤
ለዚህ ስኬት አስተዋጽኦ ለነበራችሁ ትጋት ሁሉ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። ያሳየነው ስኬት ድንቅ እና ሁላችንንም የሚያስደምም ነው፡፡ ሁላችንም ልንኮራ ይገባናል። ለመጪው በጀት ዓመት ታላቅ ስንቅ ሆኖን በላቀ ከፍታ ለመጓዝ ጠንክረን እንቀጥል፡፡
ለተሻለ ስኬት እንትጋ!
አመሰግናለሁ፡፡
አቤ ሳኖ
ፕሬዝዳንት
Comments