Logo
SeledaPost
ልዩ መረጃ‼️
የሱዳን ጦር በሱዳን ዳርፉር በኒያላ አየር ማረፊያ ሲያርፍ የነበረ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አይሮፕላን ላይ ጥቃት መሰንዘሩ ተሰማ።

የሱዳን ጦር የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አውሮፕላን በዳርፉር ግዛት ስትራቴጅካዊቷ ኒያላ ከተማ ሲያርፍ ኢላማ አድርጓል ሲል የሱዳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።

አውሮፕላኑ የኮሎምቢያ ቅጠረኛ ተዋጊዎችን ይዞ እንደነበር እና ሲያርፍ በትናንትናው ዕለት August 6/2025  በሱዳን ጦር ጥቃት እንደደረሰበት ዘገባው ጠቅሷል። በጥቃቱ ከ40 በላይ የኮሎምቢያ ቅጥረኛ ወታደሮች/Colombian mercenaries/ መሞታቸውን ዘገባው ጠቅሷል።

ኒያላ አየር ማረፊያ በጄኔራል ሀምዳን ደጋሎ በሚመራው የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ቁጥጥር ስር ይገኛል።

የሱዳን ጦር አረብ ኢምሬትስ ለሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ድጋፍ ታደርጋለች ብሎ ያምናል።

Seledadotio
Seledadotio
12 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.