የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከጋምቤላ ወደ ደምቢዶሎ ቋሚ የበረራ አገልግሎት ሊጀምር ነው
********************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሀገር ውስጥ መዳረሻዎቹን በማስፋት ከጋምቤላ ደምቢዶሎ እና ከደምቢዶሎ ጋምቤላ ቋሚ የበረራ አገልግሎት ሊጀምር መሆኑን አስታውቋል፡፡
አየር መንገዱ ይህን የበረራ አገልግሎት ከነሐሴ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚያደርግም ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎቹን አቅም በየጊዜው በማስፋት የህብረተሰቡን የእንቅስቃሴና የትራንስፖርት ፍላጎት ለማሟላት በትጋት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።
በጋምቤላ እና በደምቢዶሎ ከተሞች መካከል የሚጀመረው ይህ አዲስ የበረራ መስመር፣ በሁለቱ አካባቢዎች መካከል ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ይበልጥ ለማጠናከርና ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው አየር መንገዱ ለኢቢሲ ዶትስትሪም በሰጠው መረጃ አስታውቋል።
********************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሀገር ውስጥ መዳረሻዎቹን በማስፋት ከጋምቤላ ደምቢዶሎ እና ከደምቢዶሎ ጋምቤላ ቋሚ የበረራ አገልግሎት ሊጀምር መሆኑን አስታውቋል፡፡
አየር መንገዱ ይህን የበረራ አገልግሎት ከነሐሴ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚያደርግም ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎቹን አቅም በየጊዜው በማስፋት የህብረተሰቡን የእንቅስቃሴና የትራንስፖርት ፍላጎት ለማሟላት በትጋት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።
በጋምቤላ እና በደምቢዶሎ ከተሞች መካከል የሚጀመረው ይህ አዲስ የበረራ መስመር፣ በሁለቱ አካባቢዎች መካከል ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ይበልጥ ለማጠናከርና ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው አየር መንገዱ ለኢቢሲ ዶትስትሪም በሰጠው መረጃ አስታውቋል።
2 days ago