Logo
FBC
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) የኮሚሽኑ ሥራ የደረሰበትን ታሪካዊ ምዕራፍ አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ያነሷቸው ነጥቦች፡-

👉 ኢትዮጵያ አሳታፊና አካታች ሀገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ከገባች አራት ዓመታት ተቆጥረዋል

👉 በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ወደ ምክክር ጉባኤ የሚያደርሱ መሰረታዊ ተግባራት ተከናውነዋል

👉 በመላው ሀገሪቱ 1ሺህ 234 ወረዳዎችን ማሳተፍ ተችሏል

👉 ይህም በሀገሪቱ ካሉ አካባቢዎች 93 በመቶውን የሚሸፍን ነው

👉 በ12 ክልሎች፣ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከፌደራል ባለድርሻ አካላት ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብ ተግባር ተከናውኗል

👉 በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እንዲሳተፉ ተደርጓል

👉 አጀንዳ የተሰባሰበባቸው አካባቢዎች ለዋናው ጉባኤ የሚወክላቸውን መርጠዋል

👉 የምክር ሂደቱ ከጅምሩ አንስቶ ግልጽ፣ ገለልተኛና አሳታፊ በሆነ አሰራር እንዲመራ ተደርጓል

👉 የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሂደቱ የሰጠው ትኩረትና ያሳየው የባለቤትነት መንፈስ እጅግ የሚያበረታታ ነው

👉 የኢትዮጵያ ሕዝብ በምክክር ሂደቱ ታሪክ የማይረሳው ሀገራዊ ኃላፊነት ተወጥቷል

👉 ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በመጪው ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀመራል

👉 ጉባኤው በአዲስ አበባ ከተማ ለሦስት ተከታታይ ሳምንታት ይካሄዳል

3 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.