ሻምፒዮኑ አርሰናል ዋንጫውን የሚረከብበት ዕለት…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ22 ዓመታት በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነው አርሰናል በዛሬው ዕለት ዋንጫውን ይረከባል፡፡
ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል በዚህ ዓመት አንድ ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮን መሆኑን ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡
በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመራው የሰሜን ለንደኑ ክለብ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ የሊጉን የመጨረሻ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ከክሪስታል ፓላስ ጋር ያደርጋል፡፡
አስቀድሞ የወርቅ ጓንቱን ያሸነፈው ስፔናዊው የአርሰናል ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያ በጨዋታው ግቡን ሳያስደፍር ለመውጣት ወደ ሜዳ ይገባል።
ዴቪድ ራያ በጨዋታው ግብ የማይቆጠርበት ከሆነ በአንድ የውድድር ዓመት በሊጉ ለአርሰናል 20 ጨዋታዎች ላይ ግብ ያልተቆጠረበት ቀዳሚው ግብ ጠባቂ ይሆናል፡፡
በወድድር ዓመቱ እስካሁን በሊጉ በ19 ጨዋታዎች ግብ ያልተቆጠረበት ዴቪድ ራያ በክለቡ ታሪክ ከመድፈኞቹ የቀድሞ ግብ ጠባቂ ዳቪድ ሲማን ጋር ክብረወሰን መጋራቱ ይታወሳል፡፡
በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የቡድን ግንባታ ሒደት ከ22 ዓመታት በኋላ ከሊጉ ዋንጫ ጋር የተገናኙት መድፈኞቹ ዛሬ ምሽት በሴልኸረስት ፓርክ ዋንጫውን በክብር ይቀበላሉ፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ22 ዓመታት በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነው አርሰናል በዛሬው ዕለት ዋንጫውን ይረከባል፡፡
ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል በዚህ ዓመት አንድ ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮን መሆኑን ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡
በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመራው የሰሜን ለንደኑ ክለብ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ የሊጉን የመጨረሻ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ከክሪስታል ፓላስ ጋር ያደርጋል፡፡
አስቀድሞ የወርቅ ጓንቱን ያሸነፈው ስፔናዊው የአርሰናል ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያ በጨዋታው ግቡን ሳያስደፍር ለመውጣት ወደ ሜዳ ይገባል።
ዴቪድ ራያ በጨዋታው ግብ የማይቆጠርበት ከሆነ በአንድ የውድድር ዓመት በሊጉ ለአርሰናል 20 ጨዋታዎች ላይ ግብ ያልተቆጠረበት ቀዳሚው ግብ ጠባቂ ይሆናል፡፡
በወድድር ዓመቱ እስካሁን በሊጉ በ19 ጨዋታዎች ግብ ያልተቆጠረበት ዴቪድ ራያ በክለቡ ታሪክ ከመድፈኞቹ የቀድሞ ግብ ጠባቂ ዳቪድ ሲማን ጋር ክብረወሰን መጋራቱ ይታወሳል፡፡
በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የቡድን ግንባታ ሒደት ከ22 ዓመታት በኋላ ከሊጉ ዋንጫ ጋር የተገናኙት መድፈኞቹ ዛሬ ምሽት በሴልኸረስት ፓርክ ዋንጫውን በክብር ይቀበላሉ፡፡
2 months ago