Logo
YenetaTube
ካሪክ የማንችስተር ዩናይትድ ቋሚ አሰልጣኝ ሆኖ በይፋ ተሾመ

ማንችስተር ዩናይትድ ማይክል ካሪክን የሁለት ዓመት ውል በመስጠት የክለቡ ቋሚ አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን አረጋግጧል።

ሩበን አሞሪም በጥር ወር ከኃላፊነታቸው ከተሰናበቱ በኋላ የ44 ዓመቱ አሰልጣኝ በጊዜያዊነት ቦታውን ተረክቦ አስደናቂ ጉዞ በማድረግ ክለቡ በቻምፒዮንስ ሊግ ተሳታፊ የሚያደርገውን ቦታ እንዲያገኝ አስችሏል።

በኃላፊነት ከመራቸው 16 ጨዋታዎች ውስጥ 11ዱን አሸንፏል።

ለፕሪምየር ሊጉ የዓመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ሽልማት ከታጩ ስድስት አሰልጣኞች ዝርዝር ውስጥ ተካትቷል።

ካሪክ በጥር በጊዜያዊነት ከተሾመበት ጊዜ ጀምሮ ዩናይትድ ካሰበሰበው 36 ነጥብ በላይ ያገኘ ሌላ የሊጉ ክለብ የለም።

2 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.