Logo
SeledaPost
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኢራን "ጊዜው እያለቀ ነው" ሲሉ ማስጠንቀቃቸውን ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳየ

በመካከለኛው ምስራቅ ባለው የጂኦፖለቲካ ውጥረት ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ ለዋጋው መጨመር የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱን ለማቆም የሚደረገው ድርድር በመቀዝቀዙ ለኢራን "ጊዜው እያለቀ ነው" ሲሉ ማስጠንቀቃቸው በምክንያትነት ተጠቅሷል።
የዓለምን 20 በመቶ የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ትራንስፖርት የሚያስተናግደው የሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት፣ በአቡ ዳቢ የሚገኘው የባራካ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ አቅራቢያ በተሰነዘረ የድሮን ጥቃ እሳት መነሳ ምክንያት በነዳጅ አቅርቦት ላይ ስጋት መፍጠሩን ቢቢሲ ዘግቧል።

በዛሬው ዕለት ብሬንት የተሰኘው ድፍድፍ ነዳጅ በ1.7 በመቶ በመጨመር አንድ በርሜል በ111.13 ዶላር ደርሷል።

seledadotio
seledadotio
18 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.