Logo
EBC
የመደመር አንቀጽ

በኢንዱስትሪያዊነት ጉዞ ውስጥ፣ ዘመናዊ የአገልግሎት ዘርፍ ወሳኝ ምሰሶ በመሆን የኢንዱስትሪዎችን ስኬት ያረጋግጣል። ይህ ዘርፍ፣ ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚያቀርበው ድጋፍ እጅግ ከፍተኛ ነው። ያለው የብስለት ደረጃ የኢንዱስትሪዎችን ተወዳዳሪነት ይወስናል፡፡ እንዲሁም የራሱም ብስለት በኢንዱስትሪያዊነት ፍጥነትና ጥራት ይወሰናል።

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪያዊነት ስኬት፣ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከግብርና ወደ ዘመናዊ አምራችነት በማሸጋገር ብቻ አይወሰንም። ከዚያም አልፎ ወደ ውስብስብና እጅግ ዘመናዊ ወደ ሆነ የአገልግሎት ዘርፍ ሽግግር በማድረግም ጭምር ሊረጋገጥ ይገባል። በአሁኑ ጊዜ ዝቅተኛ የዕሴት ጭማሪ በሚያመጡ ተግባራት ላይ ያተኮረውን የአገልግሎት ዘርፍ፣ ከፍተኛ የዕሴት ጭማሪ ወዳለው የቴክኖሎጂ ምጥቀትና ውስብስብነት ማሸጋገር ወሳኝ ነው።

የመደመር መንግስት
ገፅ 207

Ethiopian Broadcasting Corporation #industry #ethiopia #medemer

1 month ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.