"ሊጉን ለማሸነፍ ለመጨረሻዎቹ አራት ጨዋታዎች ዝግጁ ነን" - ሚኬል አርቴታ
"ከኤቨርተን ጋር የምናደርገው ጨዋታ ለእኛ የፍጻሜ ጨዋታ ነው" - ፔፕ ጋርዲዮላ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዛሬ ምሽት በሚጀምረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ35ኛ ሳምንት መርሐ ግብር በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝነት ያላቸው ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ከሚቀረው ማንቼስተር ሲቲ በሦስት ነጥብ በልጦ ሊጉን እየመራ የሚገኘው አርሰናል ነገ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በኢምሬትስ ፉልሃምን ያስተናግዳል፡፡
አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ከነገው ጨዋታ በፊት በሰጡት አስተያየት፥ የሊጉን ዋንጫ ለማሸነፍ ስንቅ የሚሆን በቂ ተነሳሽነት አለን ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
የነገውን ጨዋታ ጨምሮ አራቱም ቀሪ ጨዋታዎቻችን ዋንጫውን ለማሸነፍ ወሳኝ በመሆናቸው ለእያንዳንዱ ፈተና ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡
አርሰናል በነገው ጨዋታ ፉልሃምን የሚያሸንፍ ከሆነ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ስድስት ማስፋት ይችላል፡፡
ውሃ ሰማያዊዎቹ በመጪው ሰኞ ምሽት በሂል ዲኪንሰን ስታዲየም ኤቨርተንን የሚገጥሙ ሲሆን፥ ፔፕ ጨዋታው ለእኛ የፍጻሜ ያህል ነው ብለዋል፡፡
አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በሰጡት አስተያየት፥ ከአርሰናል ጋር የስድስት ነጥብ ልዩነት ቢፈጠርም የተለየ ጫና እንደማይፈጥርባቸው ተናግረዋል፡፡
"ከኤቨርተን ጋር የምናደርገው ጨዋታ ለእኛ የፍጻሜ ጨዋታ ነው" - ፔፕ ጋርዲዮላ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዛሬ ምሽት በሚጀምረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ35ኛ ሳምንት መርሐ ግብር በዋንጫ ፉክክሩ ወሳኝነት ያላቸው ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ከሚቀረው ማንቼስተር ሲቲ በሦስት ነጥብ በልጦ ሊጉን እየመራ የሚገኘው አርሰናል ነገ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በኢምሬትስ ፉልሃምን ያስተናግዳል፡፡
አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ከነገው ጨዋታ በፊት በሰጡት አስተያየት፥ የሊጉን ዋንጫ ለማሸነፍ ስንቅ የሚሆን በቂ ተነሳሽነት አለን ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
የነገውን ጨዋታ ጨምሮ አራቱም ቀሪ ጨዋታዎቻችን ዋንጫውን ለማሸነፍ ወሳኝ በመሆናቸው ለእያንዳንዱ ፈተና ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡
አርሰናል በነገው ጨዋታ ፉልሃምን የሚያሸንፍ ከሆነ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ስድስት ማስፋት ይችላል፡፡
ውሃ ሰማያዊዎቹ በመጪው ሰኞ ምሽት በሂል ዲኪንሰን ስታዲየም ኤቨርተንን የሚገጥሙ ሲሆን፥ ፔፕ ጨዋታው ለእኛ የፍጻሜ ያህል ነው ብለዋል፡፡
አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በሰጡት አስተያየት፥ ከአርሰናል ጋር የስድስት ነጥብ ልዩነት ቢፈጠርም የተለየ ጫና እንደማይፈጥርባቸው ተናግረዋል፡፡
3 months ago