ትራምፕ በፍኖተ ሆርሙዝ የመርከቦች ጉዞን ከኢራን ጋር መቆጣጠር ይሻሉ
ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን የፍኖተ ሆርሙዝ ለመርከቦች ክፍት መሆን የተኩስ አቁሙ ስምምነት ቁልፍ ቅድመ ሁኔታ እንደነበር ገለጠች ።
እንደ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጻ፦ ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን ደሕንነት በማስጠበቅ አብረው ሊሠሩ ይችላሉ ። ይህን በተመለከተም ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሲናገሩ፦ በባሕረ ሆርሙዝ የሚያልፉ መርከቦች ደሕንነት በኢራን እና በአሜሪካ ጥበቃ እንደሚደረግላቸው ተናግረዋል ።
ፕሬዚደንቱ ለኤቢሲ ኒውስ እንደተናገሩት ከሆነ፦ የመርከቦች ደሕንነትን ለማስጠበቅ በዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን መካከል የጋራ ፕሮጄክትን ለመተግበር እያሰቡበት መሆኑንም ገልጠዋል ።
ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ሲል ኢራን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የነዳጅ እና የጋዝ ንግድ ወሳኝ መተላለፊያ የሆነውን ፍኖተ ሆርሙዝ ከከፈተች ለሁለት ሳምንታት የቦምብ ድብደባ እና ጥቃት ከመሰንዘር እንደሚቆጠቡ ገልጠው ነበር ። ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን፦ ኢራን አሁንም በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ የመርከብ ጭነቶችን መቆጣጠርዋን እንደቀጠለች መሆኑ ተዘግቧል ። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በሰጡት መግለጫ መሠረት፣ የመርከቦች ትራፊክ ፍሰት እንደቀድሞው ሁሉ «በኢራን የጦር ኃይሎች ፈቃድ» ተገዢ ሆኖ ይቀጥላል ብለዋል ።
እንደ የባህር ትራንስፖርት አገልግሎት ገለጻ ደግሞ፦ በሆርሙዝ ወሽመጥ ውስጥ የሚተላለፉ መርከቦች የትራፊክ ፍሰት ዳግም እየጨመረ ነው ።
DW Amharic
ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን የፍኖተ ሆርሙዝ ለመርከቦች ክፍት መሆን የተኩስ አቁሙ ስምምነት ቁልፍ ቅድመ ሁኔታ እንደነበር ገለጠች ።
እንደ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጻ፦ ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን ደሕንነት በማስጠበቅ አብረው ሊሠሩ ይችላሉ ። ይህን በተመለከተም ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሲናገሩ፦ በባሕረ ሆርሙዝ የሚያልፉ መርከቦች ደሕንነት በኢራን እና በአሜሪካ ጥበቃ እንደሚደረግላቸው ተናግረዋል ።
ፕሬዚደንቱ ለኤቢሲ ኒውስ እንደተናገሩት ከሆነ፦ የመርከቦች ደሕንነትን ለማስጠበቅ በዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን መካከል የጋራ ፕሮጄክትን ለመተግበር እያሰቡበት መሆኑንም ገልጠዋል ።
ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ሲል ኢራን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የነዳጅ እና የጋዝ ንግድ ወሳኝ መተላለፊያ የሆነውን ፍኖተ ሆርሙዝ ከከፈተች ለሁለት ሳምንታት የቦምብ ድብደባ እና ጥቃት ከመሰንዘር እንደሚቆጠቡ ገልጠው ነበር ። ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን፦ ኢራን አሁንም በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ የመርከብ ጭነቶችን መቆጣጠርዋን እንደቀጠለች መሆኑ ተዘግቧል ። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በሰጡት መግለጫ መሠረት፣ የመርከቦች ትራፊክ ፍሰት እንደቀድሞው ሁሉ «በኢራን የጦር ኃይሎች ፈቃድ» ተገዢ ሆኖ ይቀጥላል ብለዋል ።
እንደ የባህር ትራንስፖርት አገልግሎት ገለጻ ደግሞ፦ በሆርሙዝ ወሽመጥ ውስጥ የሚተላለፉ መርከቦች የትራፊክ ፍሰት ዳግም እየጨመረ ነው ።
DW Amharic
2 months ago