ባየርን ሙኒክ፣ ሊቨርፑል እና አትሌቲኮ ማድሪድ የሩብ ፍፃሜን ተቀላቀሉ
ትናንት ምሽት በተደረጉ የአውሮፓ ቻምፕየንስ ሊግ ጨዋታዎች ባየርን ሙኒክ አታላንታን 4 ለ 1 (በድምር ውጤት 10 ለ 2) በማሸነፍ በቀላሉ አልፏል።
ሃሪ ኬን ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር፣ ካርል እና ዲያዝ ቀሪዎቹን አክለዋል።
ሊቨርፑል በበኩሉ ጋላታሳራይን በአንፊልድ 4 ለ 0 በመርታት (በድምር 4 ለ 1) ተከታዩን ዙር ተቀላቅሏል።
ሳላህ፣ ሶቦስላይ፣ ኤኪቲኬ እና ግራቨንበርች የሊቨርፑልን ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል።
አትሌቲኮ ማድሪድ ምንም እንኳን በቶተንሃም 3 ለ 2 ቢሸነፍም፣ በመጀመሪያው ጨዋታ በነበረው 5 ለ 2 ሰፊ ውጤት ምክንያት በድምር 7 ለ 5 ማለፉን አረጋግጧል።
እነዚህ ሶስት ቡድኖች ባርሴሎና፣ ፒኤስጂ፣ ሪያል ማድሪድ፣ ስፖርቲንግ እና አርሰናልን በመቀላቀል ለታላቁ ፍልሚያ ተዘጋጅተዋል።
ትናንት ምሽት በተደረጉ የአውሮፓ ቻምፕየንስ ሊግ ጨዋታዎች ባየርን ሙኒክ አታላንታን 4 ለ 1 (በድምር ውጤት 10 ለ 2) በማሸነፍ በቀላሉ አልፏል።
ሃሪ ኬን ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር፣ ካርል እና ዲያዝ ቀሪዎቹን አክለዋል።
ሊቨርፑል በበኩሉ ጋላታሳራይን በአንፊልድ 4 ለ 0 በመርታት (በድምር 4 ለ 1) ተከታዩን ዙር ተቀላቅሏል።
ሳላህ፣ ሶቦስላይ፣ ኤኪቲኬ እና ግራቨንበርች የሊቨርፑልን ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል።
አትሌቲኮ ማድሪድ ምንም እንኳን በቶተንሃም 3 ለ 2 ቢሸነፍም፣ በመጀመሪያው ጨዋታ በነበረው 5 ለ 2 ሰፊ ውጤት ምክንያት በድምር 7 ለ 5 ማለፉን አረጋግጧል።
እነዚህ ሶስት ቡድኖች ባርሴሎና፣ ፒኤስጂ፣ ሪያል ማድሪድ፣ ስፖርቲንግ እና አርሰናልን በመቀላቀል ለታላቁ ፍልሚያ ተዘጋጅተዋል።
5 months ago