Logo
FIDEL POST NEWS
ባየርን ሙኒክ፣ ሊቨርፑል እና አትሌቲኮ ማድሪድ የሩብ ፍፃሜን ተቀላቀሉ

ትናንት ምሽት በተደረጉ የአውሮፓ ቻምፕየንስ ሊግ ጨዋታዎች ​ባየርን ሙኒክ አታላንታን 4 ለ 1 (በድምር ውጤት 10 ለ 2) በማሸነፍ በቀላሉ አልፏል።

ሃሪ ኬን ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር፣ ካርል እና ዲያዝ ቀሪዎቹን አክለዋል።

ሊቨርፑል በበኩሉ ጋላታሳራይን በአንፊልድ 4 ለ 0 በመርታት (በድምር 4 ለ 1) ተከታዩን ዙር ተቀላቅሏል።

ሳላህ፣ ሶቦስላይ፣ ኤኪቲኬ እና ግራቨንበርች የሊቨርፑልን ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል።

​አትሌቲኮ ማድሪድ ምንም እንኳን በቶተንሃም 3 ለ 2 ቢሸነፍም፣ በመጀመሪያው ጨዋታ በነበረው 5 ለ 2 ሰፊ ውጤት ምክንያት በድምር 7 ለ 5 ማለፉን አረጋግጧል።

እነዚህ ሶስት ቡድኖች ባርሴሎና፣ ፒኤስጂ፣ ሪያል ማድሪድ፣ ስፖርቲንግ እና አርሰናልን በመቀላቀል ለታላቁ ፍልሚያ ተዘጋጅተዋል።
5 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.