ሀገር አቀፍ የስፔሻል ኦሊምፒክ ውድድር ሊካሄድ ነው
#fastmereja | 11ኛው የዓለም የዳውን ሲንድሮም ቀን በኢትዮጵያ “ብቸኝነትን በአንድነት እንመክት” በሚል መሪ ቃል ከመጋቢት 4 እስከ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች እንደሚከበር ተገለጸ።
ስፔሻል ኦሊምፒክስ ኢትዮጵያ ከ“ፍቅር የኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ብሔራዊ ማኅበር” ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ይህ ሀገር አቀፍ ጨዋታ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ለሦስት ቀናት ይካሄዳል።
ዝግጅቱ ሁሉንም የኦሊምፒክ ስፖርት ዓይነቶች የሚያካትት ሲሆን፣ ውድድሩም የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ተወዳዳሪዎች ባማከለ ልዩ የስፖርት ሕግ መሠረት የሚከናወን ይሆናል።
የኢትዮጵያ ስፔሻል ኦሊምፒክ ኮሚቴ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ዕውቅና አግኝቶ ከተደራጀበት ጊዜ ጀምሮ፣ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው ዜጎች በስፖርት ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሀገር ውስጥና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር እየሠራ ይገኛል።
የፍቅር ኢትዮጵያ ማህበር የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች አስተምሮና አሰልጥኖ በማኅበሩ ውስጥ የሥራ ቅጥር እንዲያገኙ በማድረግ ጭምር አርአያነት ያለው ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት በአፍሪካና በኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው ወገኖች ላይ የሚደርሰው መገለልና መድልዎ ከፍተኛ በመሆኑ፣ እንዲህ ያሉ ስፖርታዊ መድረኮች ግንዛቤን ለመፍጠርና ብቸኝነትን ለመቀነስ ትልቅ ፋይዳ አላቸው።
#ኹነት
#fastmereja | 11ኛው የዓለም የዳውን ሲንድሮም ቀን በኢትዮጵያ “ብቸኝነትን በአንድነት እንመክት” በሚል መሪ ቃል ከመጋቢት 4 እስከ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች እንደሚከበር ተገለጸ።
ስፔሻል ኦሊምፒክስ ኢትዮጵያ ከ“ፍቅር የኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ብሔራዊ ማኅበር” ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ይህ ሀገር አቀፍ ጨዋታ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ለሦስት ቀናት ይካሄዳል።
ዝግጅቱ ሁሉንም የኦሊምፒክ ስፖርት ዓይነቶች የሚያካትት ሲሆን፣ ውድድሩም የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ተወዳዳሪዎች ባማከለ ልዩ የስፖርት ሕግ መሠረት የሚከናወን ይሆናል።
የኢትዮጵያ ስፔሻል ኦሊምፒክ ኮሚቴ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ዕውቅና አግኝቶ ከተደራጀበት ጊዜ ጀምሮ፣ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው ዜጎች በስፖርት ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሀገር ውስጥና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር እየሠራ ይገኛል።
የፍቅር ኢትዮጵያ ማህበር የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች አስተምሮና አሰልጥኖ በማኅበሩ ውስጥ የሥራ ቅጥር እንዲያገኙ በማድረግ ጭምር አርአያነት ያለው ሥራ እያከናወነ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት በአፍሪካና በኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው ወገኖች ላይ የሚደርሰው መገለልና መድልዎ ከፍተኛ በመሆኑ፣ እንዲህ ያሉ ስፖርታዊ መድረኮች ግንዛቤን ለመፍጠርና ብቸኝነትን ለመቀነስ ትልቅ ፋይዳ አላቸው።
#ኹነት
5 months ago