Logo
FIDEL POST NEWS
ትራምፕ የኢራንን ቀጣይ መሪ በመምረጥ ሂደት ላይ መሳተፍ አለብኝ ሲሉ ተናገሩ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሀገሪቱን ከፍተኛ መሪ ህልፈት ተከትሎ የኢራንን ቀጣይ መሪ በመምረጥ ረገድ በግላቸው መሳተፍ እንዳለባቸው እንደሚያምኑ ተናግረዋል። ትራምፕ ከአክሲዮስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ኢራን ያለ አሜሪካ ተሳትፎ ተተኪ ለመሾም ብትሞክር "ጊዜዋን ታባክናለች" ብለዋል።

የተገደለው የጠቅላይ መሪ አሊ ካሜኔይ ልጅ ሞጅታባ ካሜኒ በብዙዎች ዘንድ ዋንኛ ተተኪ ተደርጎ ይታያል፣ነገር ግን ትራምፕ ውጤቱን እንደማይቀበሉት ተናግረዋል። "የካሜኔይ ልጅ ቀላል ክብደህ ነው" ያሉት ትራምፕ ፤ "በሹመት ሂደት ውስጥ መሳተፍ አለብኝ" ብለዋል።

ትራምፕ የቀድሞውን አመራር ፖሊሲዎች የሚያስቀጥሉ ማንኛውንም አዲስ የኢራን መሪ እንደማይቀበሉ በመግለጽ ይህንን ማድረጉ ከአሜሪካ ጋር “በአምስት ዓመታት ውስጥ” እንደገና ግጭት እንደሚያመጣ አስጠንቅቀዋል። "የካሜኔይ ልጅ በእኔ ዘንድ ተቀባይነት የለውም፤ ለኢራን ስምምነት እና ሰላም የሚያመጣ ሰው እንፈልጋለን" ብለዋል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
5 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.