Logo
FIDEL POST NEWS
በጣሊያን የሕፃን ጠለፋ ሙከራ ያደረገው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ

​በጣሊያን ቤርጋሞ በሚገኝ አንድ የገበያ ማዕከል ውስጥ፣ አንዲት የአንድ ዓመት ሕፃን በጠራራ ጸሐይ ሊጠለፍ ሲል በፀጥታ ኃይሎች ጥረት ከሽፏል።

​ዝርዝር መረጃ፦

​ድርጊቱ፦ አንዲት እናት ከልጇ ጋር ከገበያ ማዕከሉ እየወጣች ባለችበት ወቅት፣ አንድ ግለሰብ ሕፃኗን ነጥቆ ለመሮጥ ሙከራ አድርጓል።

​አጥፊው፦ ግለሰቡ የሮማኒያ ዜግነት ያለውና መጠለያ የሌለው (Homeless) መሆኑ ተገልጿል።

​ውጤቱ፦ በማዕከሉ የነበሩ የጥበቃ ሰራተኞች በወሰዱት ፈጣን እርምጃ ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ማዋል የቻሉ ሲሆን፣ ሕፃኗም ያለምንም ጉዳት ከእናቷ ጋር ተቀላቅላለች።

​የድርጊቱ አስደንጋጭ ምስል በገበያ ማዕከሉ የክትትል ካሜራ (CCTV) ተይዟል።
4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.