Logo
FastMereja
በ202 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ

አባት አርበኛና የዕድሜ ባለጸጋ ጋኖ ጋዳቾ በ202 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡ ሥርዓተ ቀብራቸው በዛሬው ዕለት ጥር 13/2018 ዓ/ም በጮርሶ ወረዳ በቢሻ ቀበሌ ተፈጽሟል።


‎የአባተ አርቤኛ ጋኖ ጋዳቾ ሰባት ልጆችና 362 የልጅ ልጆች ነበሯቸዉ፡፡፡

‎ በ17ኛ ዓመቱ ማለትም በ1878 የጎጃም ንጉሤ ካዋ ከሞ በነገሰበት ዘመን አቶ ጋኖ ገዴቾ እስከ ጎጃም መዘመታቸው ይነገራል ።

‎የአባታቸው ውክልና በ 1914 በመውሰድ የይርጋ ጨፌ፣ የወናጎና አከባቢዎች እስከ ያበሎ፣ሀገርማሪያ፤ቡርጅ ፣ኮንሶ፤ጉጂ፣በቦራና በጌዴኦ መካከል የዘመኑን ግብር በማሰባሰብ ለ13 ዓመት ህዝብን ያገለገሉ አርበኛ አባት መሆናቸውን የታሪክ አዋቂዎች ከሟቹ አንድበት መስማታቸውን ተናግረዋል፡፡

‎አርበኛ ጋኖ ገዴቾ በአከባቢው ማህበረሰብ ትልቅ ቦታ ያላቸው፣ አስታራቂና መካሪ አባት እንደነበሩ ተጠቅሰዋል፡፡

‎ስርአተ ቀብሩ የወራዳ አመራሮች የባህል አባቶች ወዳጅ ዘመጆች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በጌዴኦ ባህላዊ ሥርዓተ ቀብራቸው በጮርሶ ወሬዳ ብሻ ቀበሌ ተፈጽሟል፡፡

ጌዴኦ ቴሌቪዥን

4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.