የቀይ ባህር እንቁ አሥመራ ሽኮሪና
የአለማችን የመጀመርያዋ የቅርስ ከተማ!
( በታዴ የማመይ ልጅ )
#ethiopia | በእርግጥም በምስራቅ በፅሎትና ቤተ ጊዮርጊስ ፣ በምዕራብ በፀራራት ፣በሰሜን በአክሪያና ባዕታ አስመራ፣ በደቡብ አዲ ጓእዳ ኮረብታዎች ደጀን የሆኗት በፅዳቷ ፣ በእርጋታዋ ፣ እንደሚፈርጥ እንቁላል በጥንቃቄ በተደረደሩት እፁብ ህንፃዎቿ በተንዠረገጉት ዘንባባዎቿ፣ የአፍሪካ ዘመናዊ ከተማ ፣የቀይ ባህር እንቁ ትመስላለች ።
በዛሬዉ የአፍታ ቱሪዝም ጉብኝታችን ባለፉት ሦስት አስርት አመታት ክፉ ክፉዉን አግዝፈው የሚነግሩን ቤኒቶ ሙሶሊኒም “ፒኮላ ሮማ” ወይም “ትንሿ ሮም” ሲል ያሞካሻት የኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ ገብተናል ።
በቆይታችን ደግነትና ባህል አክባሪነት መገለጫው ሰዉን ያለልዩነት የሚወደው ቸርነት ከባህሪዉ የሆነው የአስመራ ህዝብ አለና ወደኋላም ከመነሻዋ ወደፊትም ከገፅታዋ መለስ ቀለስ እያልን በጎዳናዎቿ ሸር ብትን እንላለንና አብራችሁን ዝለቁ ።
ጥንት ከሁለት ሺህ ዓመት በላይ ታሪክ ያለዉ አዶሊስ በዝያን ጊዜ ከነበሩ ከታወቁ የተለያዩ ሃገሮች ጋር ትልቅ የንግድ ግንኙነት የነበረዉ፤ አዶላዉያን በዝያን ጊዜ እስከ ሕንድ አልፈዉ እስከ ቻይና ግንኙነት ያደርጉባት የነበረዉ የወደብ ከተማ ናት የሰሜን ፈርጧ አስመራ።
በአሥመራ በሠምበል አካባቢ የተገኘው የአርኪዮሎጂ ማስረጃ ከተማዋ ስያሜ በ 800 ዓ.ዓ. ይወስደናል ።
የኦና ባህል ተብሎ የሚጠራውን የአሥመራ ታሪክ በ 800 ዓ.ዓ. እና በኤርትራ ትግሪኛ ቃል ባሕላዊ ታሪክ መሠረት፣ በቀበሳ አምባ ላይ በአስመራ አካባቢ አራት ጎሳዎች ይኖሩ ነበር።
በዘመኑ ተበታትነው የነበሩት ገዛ ጉርቶም። ገዛ ሽሌሌ፣ ገዛ ሴሬንሰር እና ገዛ አስመኤ የተባሉ ግዛቶች ጎሳዎች በአንድነት በመሆን ከተማ በመመስረት "አርባተ አስመራ" የሚል ስም ሰጧት ይባላል ይህም አርባተ አስመራ ማለት በትግርኛ ቋንቋ 'አራቱ ጎሳዎች' ማለት ነው።
ከባህር ጠለል በላይ ከ2,300 ሜትር በላይ ከፍታ ላይ የምትገኝ ሲሆን ከአካባቢው ዝቅተኛ ቦታዎች ሙቀት ጋር የሚቃረን መለስተኛ የአየር ንብረት ያላት አስመራ ግብፆች፤ ቱርኮች፤ጣልያኖች እንጊሊዞች ተዋግተዉባታል። ከተማዋን የጎዳ ማንም ኃይል ግን አልነበረም ወዘናዋ ዛሬም በእርጋታ ተዉቦ ይገኛል ።
ከተማዋና ዙርያዋ ታሪክ ከ 2000 ዓመት ወደኋላ ይወስደናል 2000 አመታት በላይ ስልጣኔ የነበረዉ ታሪካዉ" መጠራ በለዉ ከለዉ" የተባለ በአፍሪቃዉ ቀንድ ላይ ለሚገኙ ሁለቱም ሃገሮች የሥነ-ጽሑፍ የተከሰተበት ታሪካዊ ቦታ ሲሆን በሃዉልቱ ላይ አናባቢ የሌለዉ የግዕዝ ጽሑፍ ሰፍሮ ይገኛል ።
ሰፊ ከተማ የነበረችዉ 17 ኪሎሜትር ስፋት የነበራት ቆሃይቶ እስከ ትልቅ የአፍሪቃ ከተማ ያደርጋታል። ከዚህም ባሻገር በአፍሪቃ እስልምናን ከተቀበሉት አካባቢዎች የመጀመርያዉ የሆነው ዳህላክኬሪስ
ጥንታዊ መቃብሮች ጥንታዊ የዉኃ ማጠራቀምያ ገንዳዎች መገልገያዎች አስመራና ዙርያዋ የረጂም ታሪክ እንዳላት ህያው እማኝ ይሆናሉ ።
ይሁንና የዛሬውን ገፅታ የያዘችው በጎርጎረሳዉያኑ 1930ዎቹ በቅኝ ግዛት ኤርትራን የያዘዉ ኢጣልያዊዉ ፋሺስት ሞሶሎኒ በምስራቅ አፍሪቃ ለሚያካሂደዉ የቅኝ ግዛት ዘመቻ ማዕከል እና መነሻ እንድትሆነዉ ዓይኑን ከጣለባት በኋላ ነበር ።
የጣልያንን መምጣት ተከትሎም አስመራ የምትባለዉ ትንሽ መንደር ሞቅ ደምቅ ማለት ጀመረች ። በአፍሪካ የመጀመሪያው የቴሌቪዥን ስርጭት ፣ የመጀመሪያው Am FM አጭር መካከለኛ ረጂም ሞገድ ራዲዮ ፣
የኤርትራ የባቡር መስመር በጊንዳ ከተማ በኩል በካርሎ ካቫና መሪነት ወደ ምጽዋ የባህር ዳርቻ የሚያመራ ሀዲድ ፣ ሲኒማ
ፋብሪካዎች በብዛት ተገንብተው በአፍሪካ ምድር ላይ የአውሮፓ ዘመናዊነት እውነተኛ ማሳያ ያደርጋታል ።
ሲኒማ ኢምፔሮ፣ የፊያት ታግሊየሮ አገልግሎት ጣቢያ እና የቅዱስ ጆሴፍ ካቴድራል ያሉ ታዋቂ ሕንፃዎች ለዚህ የፈጠራ ኃይል ምስክር ናቸው። ፊያት ታግሊየሮ፣ እንደ አውሮፕላን ለመነሳት ዝግጁ የሆነ አውሮፕላን ቅርጽ ያላቸው የተጠናከረ የኮንክሪት ክንፎቹ ያሉት፣ የዘመኑን የቴክኖሎጂ፣ የእድገት እና የፍጥነት ውበት ያለውን ማራኪነት መገለጫዎች ናቸው ።
ጋዜጠኛ ጆን ጉንተር እ.ኤ.አ. በ 1955 እንደገለጸው "ጣሊያኖች [አስመራን] እንደ ትሪፖሊ በጥሩ ሁኔታ እንደገነቧት ጽፏል።
በሚያማምሩ ሰፊ ጎዳናዎች ፣ ያጌጡ የህዝብ መገልገያ ሕንፃዎች እና የሥልጣኔ ምልክት የሆነው በከተማዋ የተገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት ... የጣልያኖች የስራ ውጤት መሆኑን ጽፏል።
የኢጣሊያ መንግሥት በአስመራ እና በአስመራ ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች በኢንዱስትሪ ልማት ላይ ኢንቨስት አድርጓል ።
ከሥነ ሕንፃዋ ባሻገር፣የጂኦሜትሪክ ዲሲፕሊን እና የሜዲትራኒያን ጸጋ ድብልቅ አሰራሯ አስመራን ልዩ ውበት ይሰጣታል ።
አስመራ ሙሉ በሙሉ በዘመናዊነት ሀሳብ ዙሪያ ለተቀረፀ የከተማ ፕላን ትታወቃለች፤ ሰፊ አውራ ጎዳናዎች፣ ሥርዓታማ ሰፈሮች፣ ለጋስ የሕዝብ ቦታዎች እና ቀልጣፋ መሠረተ ልማቶች የጣልያኖች የስራ ዉጤት የተመለከተው ፋሽስት ሞሶሎኒም በዝያን ጊዜ አስመራን አፍሪቃዊትዋ ትንሽዋ የሮም ከተማ ሲል አንቆለጳጽሷታል።
ሲኒማ ቤቶቹ ራሳቸዉ ድንቅ ናቸዉ ሲኒማ ኤንፔሮ፤ ሲኒማ ዳንቴ፤ ሲኒማ ካፒቶል፤ ሲኒማ ሮማ፤ ሲኒማ ኦዲዎን የሚባሉ ሲኒማ ቤቶች አሉ።ሁሉም ሲኒማ ቤቶች የተሰሩት በአዉሮጳ ደረጃ ነዉ። ሌሎቹ ሕንጻዎች ቡናማ ሰማያዊ አረንጓዴ ቀለም ያላቸዉ ሲሆኑ የአስመራ ቅድስተ ማርያም ቤተ ክርስትያን ዉብ ቪላ ቤቶች ፤ ፋብሪካዎች አስመራ የሚገኘዉ ትልቁ መስጊድ የመሳሰሉት ሁሉ የሚያማልሉ ናቸዉ።
ከተማዋ እድለኛ ከተማም ናት 30 እና 40 ዓመት ጦርነት ተካሂዶ ከተማዋ ምንም አልተጎዳችም ከተማዋን የጎዳ ኃይል የለም። በመጀመርያ ከተማ አስመራን በኦቶማን ኤምፓየር በሚባለዉ ዘመን ቱርኩች ያዙ፤ ከዝያ በኋላ ግብጾች ያዙ ከዝያ በኋላ ጣልያኖች ያዙ ከዝያ በኋላ እንጊሊዞች ያዙ። ይህ ሁሉ ትርምስ ሲካሄድ ግን ከተማዋ አልተጎዳችም ።
የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስ እና የባህል ድርጅት አስመራ የዓለም ቅርስ ሆና እንድትመዘገብ በፖላንድ ዋርሶ ባካሔደው ጉባዔ ላይ የአለማችን የመጀመርያዋ የቅርስ ከተማ ክብር መዝገብ አስፍሯታል ።
በአስመራ የሚገኙትና ቅኝ ግዛቱ ዘመን የተሰሩት ከ 50 በላይ ሕንፃዎች በሙሉ በዓለሙ መንግሥታት የቅርስ መዝገብ በመስፈራቸዉ ኤርትራ ጥንታዊና የባህል ቅሪቶች በሙሉ የተመዘገበላት ቀዳሚዋ የዓለም ሀገር ያደርጋታል ።
UNESCO ስለ ከተማዋ ሲገልፅ
«አስመራ በጣም ዉብ የሆነች ከተማ ናት። ከሁሉ ደግሞ ሕዝብዋ በዉስጥዋ እየኖረ ባህሉን እየጠበቀ ሥነ ሕንጻዉን እየጠበቀ በመሆኑ ነዉ። የአስመራ ሕንጻዎች ለየት ያለ ንድፍና ቅርስ የያዙ ናቸዉ። ጣልያኖቹ በቅኝ ግዛት ወቅት ሃገራቸዉ ዉስጥ የሌለ ነጻነት አስመራ ዉስጥ፤ ቅኝ ሃገር ዉስጥ ነጻነት ተሰምቶአቸዉ ፤ በምህንድስናዉ ረገድ አብዮት ያካሄዱ ይመስላል። ምክንያቱም ኢጣልያ ዉስጥ የማይገኘዉ ሕንጻ አስመራ ዉስጥ አለ።» ሲል ገልጿል ።
አስመራ ከተማ በኪነ ሕንጻ ብቻ ሳይሆን በጽዳትዋ ፤ በአየር ፀባይዋና በተለያዩ ሁኔታዎች ከአፍሪቃ የታወቁ ከተማ በመሆንዋ አስመራ በዓለሙ የቅርስ መዝገብ መመዝገብዋ ለኛ ለኢትዮጵያዉያን ለዓለም ሕዝብ ሁሉ ኩራት ነዉ ሲሉ የወቅቱ የበኢትዮጵያ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ገልጿል ።
አስመራ ሕያው ሙዚየም እና ሕያው የስልጣኔ ከተማ የአፍሪካን ዘመናዊነት ማሳያ የተረጋጋች እጅግ ማራኪ ብትሆንም ከተማዋ ከቱሪዝም ዘርፉ ተጠቃሚ አልሆነችም።
ሜሳረጊያዉን የባለቅኔዉን የሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን ግጥም እንገባበዝና ለዛሬው ይብቃን ።
አስመራ
ምነው ሁሉ እንዳንቺ አስመራ
እንደ ከተሞች መዲና አቀያየሱ ቢጠራ
ያውራ ጎዳናሽ ጠለላ ፡
ሁሉን በአክናፉ እየጠራ
አስር ሰዓት ላይ ሲደራ
ለመንገደኛሽ መዝናኛ ፣ሲያጠላ ሲያብብ ሲያፈራ
ምነው ሁሉ እንዳንቺ አስመራ
አደባባይ ሲያነጥፉ
አድባራትና መስኪዱን ፣ ካቴድራሉን በየረድፉ
ገበያውን በየመልኩ ፣ እንደ አውታር እያሰለፉ
በወግ እየደረደሩ ፣በስምረት እያሰመሩ
በውበት እያዳበሩ ፣እያሳመሩ ቢያደሩ
በየክፍሉ በየበሩ በየመልኩ በየተራ
ፋኖሱን እንደ ደመራ
ቡና ቤቱን እንደ ሦራ
ምነው ሁሉ እንደ አንቺ አስመራ
እንደ ከተሞች መዲና አቀያየሱ ቢጠራ፡፡
እሳት ወይ አበባ (ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን )
የአለማችን የመጀመርያዋ የቅርስ ከተማ!
( በታዴ የማመይ ልጅ )
#ethiopia | በእርግጥም በምስራቅ በፅሎትና ቤተ ጊዮርጊስ ፣ በምዕራብ በፀራራት ፣በሰሜን በአክሪያና ባዕታ አስመራ፣ በደቡብ አዲ ጓእዳ ኮረብታዎች ደጀን የሆኗት በፅዳቷ ፣ በእርጋታዋ ፣ እንደሚፈርጥ እንቁላል በጥንቃቄ በተደረደሩት እፁብ ህንፃዎቿ በተንዠረገጉት ዘንባባዎቿ፣ የአፍሪካ ዘመናዊ ከተማ ፣የቀይ ባህር እንቁ ትመስላለች ።
በዛሬዉ የአፍታ ቱሪዝም ጉብኝታችን ባለፉት ሦስት አስርት አመታት ክፉ ክፉዉን አግዝፈው የሚነግሩን ቤኒቶ ሙሶሊኒም “ፒኮላ ሮማ” ወይም “ትንሿ ሮም” ሲል ያሞካሻት የኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ ገብተናል ።
በቆይታችን ደግነትና ባህል አክባሪነት መገለጫው ሰዉን ያለልዩነት የሚወደው ቸርነት ከባህሪዉ የሆነው የአስመራ ህዝብ አለና ወደኋላም ከመነሻዋ ወደፊትም ከገፅታዋ መለስ ቀለስ እያልን በጎዳናዎቿ ሸር ብትን እንላለንና አብራችሁን ዝለቁ ።
ጥንት ከሁለት ሺህ ዓመት በላይ ታሪክ ያለዉ አዶሊስ በዝያን ጊዜ ከነበሩ ከታወቁ የተለያዩ ሃገሮች ጋር ትልቅ የንግድ ግንኙነት የነበረዉ፤ አዶላዉያን በዝያን ጊዜ እስከ ሕንድ አልፈዉ እስከ ቻይና ግንኙነት ያደርጉባት የነበረዉ የወደብ ከተማ ናት የሰሜን ፈርጧ አስመራ።
በአሥመራ በሠምበል አካባቢ የተገኘው የአርኪዮሎጂ ማስረጃ ከተማዋ ስያሜ በ 800 ዓ.ዓ. ይወስደናል ።
የኦና ባህል ተብሎ የሚጠራውን የአሥመራ ታሪክ በ 800 ዓ.ዓ. እና በኤርትራ ትግሪኛ ቃል ባሕላዊ ታሪክ መሠረት፣ በቀበሳ አምባ ላይ በአስመራ አካባቢ አራት ጎሳዎች ይኖሩ ነበር።
በዘመኑ ተበታትነው የነበሩት ገዛ ጉርቶም። ገዛ ሽሌሌ፣ ገዛ ሴሬንሰር እና ገዛ አስመኤ የተባሉ ግዛቶች ጎሳዎች በአንድነት በመሆን ከተማ በመመስረት "አርባተ አስመራ" የሚል ስም ሰጧት ይባላል ይህም አርባተ አስመራ ማለት በትግርኛ ቋንቋ 'አራቱ ጎሳዎች' ማለት ነው።
ከባህር ጠለል በላይ ከ2,300 ሜትር በላይ ከፍታ ላይ የምትገኝ ሲሆን ከአካባቢው ዝቅተኛ ቦታዎች ሙቀት ጋር የሚቃረን መለስተኛ የአየር ንብረት ያላት አስመራ ግብፆች፤ ቱርኮች፤ጣልያኖች እንጊሊዞች ተዋግተዉባታል። ከተማዋን የጎዳ ማንም ኃይል ግን አልነበረም ወዘናዋ ዛሬም በእርጋታ ተዉቦ ይገኛል ።
ከተማዋና ዙርያዋ ታሪክ ከ 2000 ዓመት ወደኋላ ይወስደናል 2000 አመታት በላይ ስልጣኔ የነበረዉ ታሪካዉ" መጠራ በለዉ ከለዉ" የተባለ በአፍሪቃዉ ቀንድ ላይ ለሚገኙ ሁለቱም ሃገሮች የሥነ-ጽሑፍ የተከሰተበት ታሪካዊ ቦታ ሲሆን በሃዉልቱ ላይ አናባቢ የሌለዉ የግዕዝ ጽሑፍ ሰፍሮ ይገኛል ።
ሰፊ ከተማ የነበረችዉ 17 ኪሎሜትር ስፋት የነበራት ቆሃይቶ እስከ ትልቅ የአፍሪቃ ከተማ ያደርጋታል። ከዚህም ባሻገር በአፍሪቃ እስልምናን ከተቀበሉት አካባቢዎች የመጀመርያዉ የሆነው ዳህላክኬሪስ
ጥንታዊ መቃብሮች ጥንታዊ የዉኃ ማጠራቀምያ ገንዳዎች መገልገያዎች አስመራና ዙርያዋ የረጂም ታሪክ እንዳላት ህያው እማኝ ይሆናሉ ።
ይሁንና የዛሬውን ገፅታ የያዘችው በጎርጎረሳዉያኑ 1930ዎቹ በቅኝ ግዛት ኤርትራን የያዘዉ ኢጣልያዊዉ ፋሺስት ሞሶሎኒ በምስራቅ አፍሪቃ ለሚያካሂደዉ የቅኝ ግዛት ዘመቻ ማዕከል እና መነሻ እንድትሆነዉ ዓይኑን ከጣለባት በኋላ ነበር ።
የጣልያንን መምጣት ተከትሎም አስመራ የምትባለዉ ትንሽ መንደር ሞቅ ደምቅ ማለት ጀመረች ። በአፍሪካ የመጀመሪያው የቴሌቪዥን ስርጭት ፣ የመጀመሪያው Am FM አጭር መካከለኛ ረጂም ሞገድ ራዲዮ ፣
የኤርትራ የባቡር መስመር በጊንዳ ከተማ በኩል በካርሎ ካቫና መሪነት ወደ ምጽዋ የባህር ዳርቻ የሚያመራ ሀዲድ ፣ ሲኒማ
ፋብሪካዎች በብዛት ተገንብተው በአፍሪካ ምድር ላይ የአውሮፓ ዘመናዊነት እውነተኛ ማሳያ ያደርጋታል ።
ሲኒማ ኢምፔሮ፣ የፊያት ታግሊየሮ አገልግሎት ጣቢያ እና የቅዱስ ጆሴፍ ካቴድራል ያሉ ታዋቂ ሕንፃዎች ለዚህ የፈጠራ ኃይል ምስክር ናቸው። ፊያት ታግሊየሮ፣ እንደ አውሮፕላን ለመነሳት ዝግጁ የሆነ አውሮፕላን ቅርጽ ያላቸው የተጠናከረ የኮንክሪት ክንፎቹ ያሉት፣ የዘመኑን የቴክኖሎጂ፣ የእድገት እና የፍጥነት ውበት ያለውን ማራኪነት መገለጫዎች ናቸው ።
ጋዜጠኛ ጆን ጉንተር እ.ኤ.አ. በ 1955 እንደገለጸው "ጣሊያኖች [አስመራን] እንደ ትሪፖሊ በጥሩ ሁኔታ እንደገነቧት ጽፏል።
በሚያማምሩ ሰፊ ጎዳናዎች ፣ ያጌጡ የህዝብ መገልገያ ሕንፃዎች እና የሥልጣኔ ምልክት የሆነው በከተማዋ የተገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት ... የጣልያኖች የስራ ውጤት መሆኑን ጽፏል።
የኢጣሊያ መንግሥት በአስመራ እና በአስመራ ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች በኢንዱስትሪ ልማት ላይ ኢንቨስት አድርጓል ።
ከሥነ ሕንፃዋ ባሻገር፣የጂኦሜትሪክ ዲሲፕሊን እና የሜዲትራኒያን ጸጋ ድብልቅ አሰራሯ አስመራን ልዩ ውበት ይሰጣታል ።
አስመራ ሙሉ በሙሉ በዘመናዊነት ሀሳብ ዙሪያ ለተቀረፀ የከተማ ፕላን ትታወቃለች፤ ሰፊ አውራ ጎዳናዎች፣ ሥርዓታማ ሰፈሮች፣ ለጋስ የሕዝብ ቦታዎች እና ቀልጣፋ መሠረተ ልማቶች የጣልያኖች የስራ ዉጤት የተመለከተው ፋሽስት ሞሶሎኒም በዝያን ጊዜ አስመራን አፍሪቃዊትዋ ትንሽዋ የሮም ከተማ ሲል አንቆለጳጽሷታል።
ሲኒማ ቤቶቹ ራሳቸዉ ድንቅ ናቸዉ ሲኒማ ኤንፔሮ፤ ሲኒማ ዳንቴ፤ ሲኒማ ካፒቶል፤ ሲኒማ ሮማ፤ ሲኒማ ኦዲዎን የሚባሉ ሲኒማ ቤቶች አሉ።ሁሉም ሲኒማ ቤቶች የተሰሩት በአዉሮጳ ደረጃ ነዉ። ሌሎቹ ሕንጻዎች ቡናማ ሰማያዊ አረንጓዴ ቀለም ያላቸዉ ሲሆኑ የአስመራ ቅድስተ ማርያም ቤተ ክርስትያን ዉብ ቪላ ቤቶች ፤ ፋብሪካዎች አስመራ የሚገኘዉ ትልቁ መስጊድ የመሳሰሉት ሁሉ የሚያማልሉ ናቸዉ።
ከተማዋ እድለኛ ከተማም ናት 30 እና 40 ዓመት ጦርነት ተካሂዶ ከተማዋ ምንም አልተጎዳችም ከተማዋን የጎዳ ኃይል የለም። በመጀመርያ ከተማ አስመራን በኦቶማን ኤምፓየር በሚባለዉ ዘመን ቱርኩች ያዙ፤ ከዝያ በኋላ ግብጾች ያዙ ከዝያ በኋላ ጣልያኖች ያዙ ከዝያ በኋላ እንጊሊዞች ያዙ። ይህ ሁሉ ትርምስ ሲካሄድ ግን ከተማዋ አልተጎዳችም ።
የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስ እና የባህል ድርጅት አስመራ የዓለም ቅርስ ሆና እንድትመዘገብ በፖላንድ ዋርሶ ባካሔደው ጉባዔ ላይ የአለማችን የመጀመርያዋ የቅርስ ከተማ ክብር መዝገብ አስፍሯታል ።
በአስመራ የሚገኙትና ቅኝ ግዛቱ ዘመን የተሰሩት ከ 50 በላይ ሕንፃዎች በሙሉ በዓለሙ መንግሥታት የቅርስ መዝገብ በመስፈራቸዉ ኤርትራ ጥንታዊና የባህል ቅሪቶች በሙሉ የተመዘገበላት ቀዳሚዋ የዓለም ሀገር ያደርጋታል ።
UNESCO ስለ ከተማዋ ሲገልፅ
«አስመራ በጣም ዉብ የሆነች ከተማ ናት። ከሁሉ ደግሞ ሕዝብዋ በዉስጥዋ እየኖረ ባህሉን እየጠበቀ ሥነ ሕንጻዉን እየጠበቀ በመሆኑ ነዉ። የአስመራ ሕንጻዎች ለየት ያለ ንድፍና ቅርስ የያዙ ናቸዉ። ጣልያኖቹ በቅኝ ግዛት ወቅት ሃገራቸዉ ዉስጥ የሌለ ነጻነት አስመራ ዉስጥ፤ ቅኝ ሃገር ዉስጥ ነጻነት ተሰምቶአቸዉ ፤ በምህንድስናዉ ረገድ አብዮት ያካሄዱ ይመስላል። ምክንያቱም ኢጣልያ ዉስጥ የማይገኘዉ ሕንጻ አስመራ ዉስጥ አለ።» ሲል ገልጿል ።
አስመራ ከተማ በኪነ ሕንጻ ብቻ ሳይሆን በጽዳትዋ ፤ በአየር ፀባይዋና በተለያዩ ሁኔታዎች ከአፍሪቃ የታወቁ ከተማ በመሆንዋ አስመራ በዓለሙ የቅርስ መዝገብ መመዝገብዋ ለኛ ለኢትዮጵያዉያን ለዓለም ሕዝብ ሁሉ ኩራት ነዉ ሲሉ የወቅቱ የበኢትዮጵያ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ገልጿል ።
አስመራ ሕያው ሙዚየም እና ሕያው የስልጣኔ ከተማ የአፍሪካን ዘመናዊነት ማሳያ የተረጋጋች እጅግ ማራኪ ብትሆንም ከተማዋ ከቱሪዝም ዘርፉ ተጠቃሚ አልሆነችም።
ሜሳረጊያዉን የባለቅኔዉን የሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን ግጥም እንገባበዝና ለዛሬው ይብቃን ።
አስመራ
ምነው ሁሉ እንዳንቺ አስመራ
እንደ ከተሞች መዲና አቀያየሱ ቢጠራ
ያውራ ጎዳናሽ ጠለላ ፡
ሁሉን በአክናፉ እየጠራ
አስር ሰዓት ላይ ሲደራ
ለመንገደኛሽ መዝናኛ ፣ሲያጠላ ሲያብብ ሲያፈራ
ምነው ሁሉ እንዳንቺ አስመራ
አደባባይ ሲያነጥፉ
አድባራትና መስኪዱን ፣ ካቴድራሉን በየረድፉ
ገበያውን በየመልኩ ፣ እንደ አውታር እያሰለፉ
በወግ እየደረደሩ ፣በስምረት እያሰመሩ
በውበት እያዳበሩ ፣እያሳመሩ ቢያደሩ
በየክፍሉ በየበሩ በየመልኩ በየተራ
ፋኖሱን እንደ ደመራ
ቡና ቤቱን እንደ ሦራ
ምነው ሁሉ እንደ አንቺ አስመራ
እንደ ከተሞች መዲና አቀያየሱ ቢጠራ፡፡
እሳት ወይ አበባ (ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን )
8 months ago