በሀበሻ ባህር ዓለምአቀፋዊ ውድድር !
(የሀብታሙ ደባሱ አዲሱ የግል ሀሳብ)
#ethiopia | በዛሬው ነገረ-ሀሳቤ በታሪክ ውስጥ የሀበሻ ባህር ተብሎ ስለሚጠራው እና ቀይ ባህር ላይ ያተኩራል ።በትውልድ ውስጥ ዘላለማዊ አሻራ ማሳረፍ ( Permanent Interest ) ዘላቂ እና ታሪክ የማይረሳው ተግባር ነው፤ ይህ ለእኛ ለእኔ ዘመን ትውልድ ትልቅ እድል ነው።
ቀይ ባህር በዓለም አቀፍ ደረጃ ቁልፍ ከሆኑ የንግድ እና የስትራቴጂክ የውሃ መስመሮች መካከል አንዱ ሲሆን (ለምሳሌ፡ በስዊዝ ካናል እና በባብ ኤል-ማንደብ በኩል) በመሆኑም የዓለምና የቃጣናው ኃያላን ሀገራት ትኩረት የሚስብ የጂኦፖለቲካል ውድድር ማዕከል ሆኗል።
ይህ ውድድር የንግድ ፍሰትን ከመቆጣጠር እስከ ወታደራዊ መንደሮች ማስፋፋት ድረስ የተዘረጋ ሲሆን፣ እንደ ጂቡቲ ባሉ አካባቢዎች የቻይና፣ የአሜሪካ፣ የፈረንሳይ፣ የጃፓን እና የዐረብ ሀገራት ወታደራዊ መንደሮች መገንባታቸው የውድድሩን መጠን ያሳያል። (ምንጭ፡ The International Politics of the Red Sea እና ሌሎች ጽሑፎች) በዚህ ውስብስብ ዓለምአቀፋዊ ውድድር ውስጥ፣ "ኢትዮጵያ" ቁልፍ ሚና ያላት ሀገር ናት ።
🔴የኢትዮጵያ ሚና፦
ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላት ሚና በበርካታ ምሁራዊ ስራዎች ተንጸባርቋል፤ በተለይም በ"Ethiopia and the Red Sea: The Rise and Decline of the Solomonic Dynasty" በሞርደካይ አቢር (Mordechai Abir) እና በቅርብ ጊዜ በተሰሩ ጥናቶች ላይ። እነዚህ ማጣቀሻዎች የኢትዮጵያን ሚና በሦስት ዋና ዋና ገጽታዎች ይመረምራሉ፦
🔴 ታሪካዊ እና የህልውና ጥያቄ፦
እንደ አቢር እና ሌሎች የታሪክ ተመራማሪዎች ገለጻ፣የኢትዮጵያ ስልጣኔ (ለምሳሌ አክሱም) እና ኢኮኖሚ ከጥንት ጀምሮ ከቀይ ባህር ጋር የተቆራኘ ነው። ኢትዮጵያ እስከ 1993 እ.ኤ.አ. (ኤርትራ ነፃ እስከወጣችበት ጊዜ) ድረስ የባህር በር ነበራት፤ ቀይ ባህርም ቀደም ባሉት ዘመናት "የሀበሻ ባህር" ተብሎ ይጠራ እንደነበር ይታወቃል።(ምንጭ፡ ረዳት ፕሮፌሰር አደም ካሚል እና ሌሎች)
አሁን ያላት የየብስ የተከበበች ሀገር (Landlocked country) አቋም ከፍተኛ የሆነ የንግድና የሎጂስቲክስ ጥገኝነት (በተለይ በጅቡቲ ወደቦች ላይ) እንዲፈጠር አድርጓል።
መንግስት የቀይ ባህርን መዳረሻ እንደ "የህልውና ጉዳይ" መመልከቱ፣ ይህም ታሪካዊ መብቶችን እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለማረጋገጥ መሆኑን ያመለክታል። (ምንጭ፡-ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ በህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት የተናገሩት ንግግሮች፣ "Ethiopia's Red Sea Politics" - Biruk Terrefe) መጽሐፍ መመልከት ይቻላል ።
🔴የሎጂስቲክስ እና ኢኮኖሚያዊ ስትራቴጂ:-
የኢትዮጵያ የንግድ ኮሪደሮች ለሀገር ውስጥ የሚገቡና የሚወጡ ሸቀጦች መተላለፊያ ብቻ ሳይሆኑ፣ የቃጣናው፣የአገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ተዋናዮች የሉዓላዊነት እና የደህንነት ራዕያቸውን የሚደራደሩበት ወሳኝ መድረኮች ናቸው። (ምንጭ፡ "Ethiopia's Red Sea Politics: Corridors, Ports and Security in the Horn of Africa")የሀገሪቱን የሎጂስቲክስ ወጪ ለመቀነስ እና የንግድ ደህንነትን ለማረጋገጥ በርካታ አማራጭ የወደብ መዳረሻዎችን መፈለጓ የአገሪቱን ሰፋ ያለ የዓለም አቀፍ ደረጃ ላይ ያላትን ተዕጽኖ ፈጣሪነትናራዕይ አካል እንደሆነ አሳይታለች ።
🔴የቃጣናዊ ደህንነት፦
ኢትዮጵያ ጥንካሬ እና ድክመት በቀይ ባህር ጂኦፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ተጽዕኖ አለው።በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ የህዝብ ብዛት እና ኢኮኖሚ ያለን ሀገር እንደመሆናችን፣የውስጥ መረጋጋቷ የቀይ ባህርን ጨምሮ ለቀጣናው ደህንነት ወሳኝ ነው።
ከ"ቀይ ባህር ፎረም"(The Red Sea Forum) መገለል ኢትዮጵያ በቀይ ባህር አዋሳኝ ሀገራት ከተመሰረተው ውጭ መደረጓ ተገቢ እንዳልሆነ በተደጋጋሚ አስታውቃለች። ይህ ደግሞ በባህር ደህንነት እና ትብብር ዙሪያ በቃጣናዊ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ ያላትን ሙሉ ሚና ለመጫወት ያላትን ፍላጎት ያሳያል።የቀይ ባህር መድረክ አባለ ሀገራት ለግንዛቤ (ግብፅ፣ሳውዲ አረቢያ ፣ጆርዳን፣የመን፣ሱዳን ፣ኤርትራ ፣ጅቡቲ እና ሱማሊያ ናቸው)
🖊እንደ መውጫ ⁉️
በቀይ ባህር ዙሪያ ያለው ዓለም አቀፋዊ ውድድር በኃያላን ሀገራት የወታደራዊ መንደር ማስፋፋት እና በቃጣናዊ ሀገራት መካከል ባለው የሉዓላዊነትና የኢኮኖሚ ጥቅም ጥበቃ የተሞላ ነው። በዚህ ሁኔታ ውስጥ የኢትዮጵያ ሚና ከታሪካዊ መብቷ በመነሳት፣ የባህር በር መዳረሻ የማግኘት የህልውና ጥያቄዋን ከማረጋገጥ እንዲሁም ለቃጣናዊ ደህንነትና ልማት አስተዋጽኦ ከማድረግ ጋር የተያያዘ ነው።
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መሳካት የድርሻዬን እወጣለሁ !
#ethiopia 🇪🇹
ለበለጠ ወዳጅነት የፃሃፊውን የኤክስ(X) እና የፌስቡክ ገፅ ይከታተሉ :-
🔗የኤክስ(X)ገፅ:-https://x.com/HDebasu?t=eR...
🔗የፌስቡክ:-https://www.facebook.com/s...
(የሀብታሙ ደባሱ አዲሱ የግል ሀሳብ)
#ethiopia | በዛሬው ነገረ-ሀሳቤ በታሪክ ውስጥ የሀበሻ ባህር ተብሎ ስለሚጠራው እና ቀይ ባህር ላይ ያተኩራል ።በትውልድ ውስጥ ዘላለማዊ አሻራ ማሳረፍ ( Permanent Interest ) ዘላቂ እና ታሪክ የማይረሳው ተግባር ነው፤ ይህ ለእኛ ለእኔ ዘመን ትውልድ ትልቅ እድል ነው።
ቀይ ባህር በዓለም አቀፍ ደረጃ ቁልፍ ከሆኑ የንግድ እና የስትራቴጂክ የውሃ መስመሮች መካከል አንዱ ሲሆን (ለምሳሌ፡ በስዊዝ ካናል እና በባብ ኤል-ማንደብ በኩል) በመሆኑም የዓለምና የቃጣናው ኃያላን ሀገራት ትኩረት የሚስብ የጂኦፖለቲካል ውድድር ማዕከል ሆኗል።
ይህ ውድድር የንግድ ፍሰትን ከመቆጣጠር እስከ ወታደራዊ መንደሮች ማስፋፋት ድረስ የተዘረጋ ሲሆን፣ እንደ ጂቡቲ ባሉ አካባቢዎች የቻይና፣ የአሜሪካ፣ የፈረንሳይ፣ የጃፓን እና የዐረብ ሀገራት ወታደራዊ መንደሮች መገንባታቸው የውድድሩን መጠን ያሳያል። (ምንጭ፡ The International Politics of the Red Sea እና ሌሎች ጽሑፎች) በዚህ ውስብስብ ዓለምአቀፋዊ ውድድር ውስጥ፣ "ኢትዮጵያ" ቁልፍ ሚና ያላት ሀገር ናት ።
🔴የኢትዮጵያ ሚና፦
ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ጂኦፖለቲካ ውስጥ ያላት ሚና በበርካታ ምሁራዊ ስራዎች ተንጸባርቋል፤ በተለይም በ"Ethiopia and the Red Sea: The Rise and Decline of the Solomonic Dynasty" በሞርደካይ አቢር (Mordechai Abir) እና በቅርብ ጊዜ በተሰሩ ጥናቶች ላይ። እነዚህ ማጣቀሻዎች የኢትዮጵያን ሚና በሦስት ዋና ዋና ገጽታዎች ይመረምራሉ፦
🔴 ታሪካዊ እና የህልውና ጥያቄ፦
እንደ አቢር እና ሌሎች የታሪክ ተመራማሪዎች ገለጻ፣የኢትዮጵያ ስልጣኔ (ለምሳሌ አክሱም) እና ኢኮኖሚ ከጥንት ጀምሮ ከቀይ ባህር ጋር የተቆራኘ ነው። ኢትዮጵያ እስከ 1993 እ.ኤ.አ. (ኤርትራ ነፃ እስከወጣችበት ጊዜ) ድረስ የባህር በር ነበራት፤ ቀይ ባህርም ቀደም ባሉት ዘመናት "የሀበሻ ባህር" ተብሎ ይጠራ እንደነበር ይታወቃል።(ምንጭ፡ ረዳት ፕሮፌሰር አደም ካሚል እና ሌሎች)
አሁን ያላት የየብስ የተከበበች ሀገር (Landlocked country) አቋም ከፍተኛ የሆነ የንግድና የሎጂስቲክስ ጥገኝነት (በተለይ በጅቡቲ ወደቦች ላይ) እንዲፈጠር አድርጓል።
መንግስት የቀይ ባህርን መዳረሻ እንደ "የህልውና ጉዳይ" መመልከቱ፣ ይህም ታሪካዊ መብቶችን እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለማረጋገጥ መሆኑን ያመለክታል። (ምንጭ፡-ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ በህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት የተናገሩት ንግግሮች፣ "Ethiopia's Red Sea Politics" - Biruk Terrefe) መጽሐፍ መመልከት ይቻላል ።
🔴የሎጂስቲክስ እና ኢኮኖሚያዊ ስትራቴጂ:-
የኢትዮጵያ የንግድ ኮሪደሮች ለሀገር ውስጥ የሚገቡና የሚወጡ ሸቀጦች መተላለፊያ ብቻ ሳይሆኑ፣ የቃጣናው፣የአገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ተዋናዮች የሉዓላዊነት እና የደህንነት ራዕያቸውን የሚደራደሩበት ወሳኝ መድረኮች ናቸው። (ምንጭ፡ "Ethiopia's Red Sea Politics: Corridors, Ports and Security in the Horn of Africa")የሀገሪቱን የሎጂስቲክስ ወጪ ለመቀነስ እና የንግድ ደህንነትን ለማረጋገጥ በርካታ አማራጭ የወደብ መዳረሻዎችን መፈለጓ የአገሪቱን ሰፋ ያለ የዓለም አቀፍ ደረጃ ላይ ያላትን ተዕጽኖ ፈጣሪነትናራዕይ አካል እንደሆነ አሳይታለች ።
🔴የቃጣናዊ ደህንነት፦
ኢትዮጵያ ጥንካሬ እና ድክመት በቀይ ባህር ጂኦፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ተጽዕኖ አለው።በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ የህዝብ ብዛት እና ኢኮኖሚ ያለን ሀገር እንደመሆናችን፣የውስጥ መረጋጋቷ የቀይ ባህርን ጨምሮ ለቀጣናው ደህንነት ወሳኝ ነው።
ከ"ቀይ ባህር ፎረም"(The Red Sea Forum) መገለል ኢትዮጵያ በቀይ ባህር አዋሳኝ ሀገራት ከተመሰረተው ውጭ መደረጓ ተገቢ እንዳልሆነ በተደጋጋሚ አስታውቃለች። ይህ ደግሞ በባህር ደህንነት እና ትብብር ዙሪያ በቃጣናዊ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ ያላትን ሙሉ ሚና ለመጫወት ያላትን ፍላጎት ያሳያል።የቀይ ባህር መድረክ አባለ ሀገራት ለግንዛቤ (ግብፅ፣ሳውዲ አረቢያ ፣ጆርዳን፣የመን፣ሱዳን ፣ኤርትራ ፣ጅቡቲ እና ሱማሊያ ናቸው)
🖊እንደ መውጫ ⁉️
በቀይ ባህር ዙሪያ ያለው ዓለም አቀፋዊ ውድድር በኃያላን ሀገራት የወታደራዊ መንደር ማስፋፋት እና በቃጣናዊ ሀገራት መካከል ባለው የሉዓላዊነትና የኢኮኖሚ ጥቅም ጥበቃ የተሞላ ነው። በዚህ ሁኔታ ውስጥ የኢትዮጵያ ሚና ከታሪካዊ መብቷ በመነሳት፣ የባህር በር መዳረሻ የማግኘት የህልውና ጥያቄዋን ከማረጋገጥ እንዲሁም ለቃጣናዊ ደህንነትና ልማት አስተዋጽኦ ከማድረግ ጋር የተያያዘ ነው።
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መሳካት የድርሻዬን እወጣለሁ !
#ethiopia 🇪🇹
ለበለጠ ወዳጅነት የፃሃፊውን የኤክስ(X) እና የፌስቡክ ገፅ ይከታተሉ :-
🔗የኤክስ(X)ገፅ:-https://x.com/HDebasu?t=eR...
🔗የፌስቡክ:-https://www.facebook.com/s...
9 months ago