"አገሬ ለኔ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን እኔ ለአገሬ ምን አደረኩላት ብለን እንጠይቅ?!" 🇺🇸
#ethiopia | በደቡብ ቴክሳስ ዳላስ ከተማ፤ በተተኮሰባቸው ጥይት የተገደሉት ፕሬዚደንት ኬኔዲ ሥፍራ ቆሚያለሁ።
የቀድሞው ዝነኛና ተወዳጁ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ በቴክሳስ ግዛት፣ ዳላስ ከተማ፣ በክፍት መኪና፤ በጉብኝት ሳሉ ነበር እኤአ በኅዳር 22፣ 1963 ቀትር ላይ በደቡብ ቴክሳስ ዳላስ ከተማ፤ በተተኮሰባቸው ጥይት የተገደሉት። ፕሬዚደንት ኬኔዲ ስልጣን ላይ ከወጡ ሦስተኛ ዓመታቸን ሊይዙ ትንሽ ወራት ይቀራቸው ነበር።
ከዚያች ቅጽበት ጀምሮ ሰውየውን ( ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ ) ማን ገደላቸው? ... ለምን ተገደሉ? ... በሚለው ዙርያ ሺህ ምርመራዎች ተደርገዋል።
እነዚህ የምርመራ ሂደቱን የያዙ ዶሴዎችም በምሥጢር ሲከማቹ ነው የኖሩት።
የ1964 የእውነት አፈላላጊው ‘ዋረን ኮሚሽን’ ፕሬዝዳንት ኬኔዲ የተገደሉት ሊ ሐርቬይ ኦስዋልድ በተባለ ግለሰብ ነው ብሎ ነበር።
ሊ ሐርቬይ ቀደም ሲል በሶቭየት ኅብረት ለአጭር ጊዜ የኖረ አሜሪካዊ ሲሆን ድርጊቱን የፈጸመውም በግሉ ነው ተብሎ ነበር።
በቁጥጥር ሥር በዋለ በሁለተኛው ቀን ግን ብዙም ግልጽ ባልሆነ መንገድ በዳላስ ፖሊስ ምድር ቤት ውስጥ ተገድሏል።
ይሁንና የኬኔዲ አገዳደል፣ ገዳያቸው ነበር የተባለው ሰው በፖሊስ ምድር ቤት መገደል ምሥጢርና ተያያዥ ጉዳዮች ለዐሥርታት ለብዙ መላምቶች ክፍት ሆኖ ቆይቷል።
የሴራ ፖለቲካ ተንታኞች ደግሞ ግድያውንና ግድያውን ተከትሎ የሆነውን ነገር ሁሉ የተለያዩ ትርጉም ሲሰጡት ኖረዋል። ዛሬም ድረስ ...
አንዳንዶች ወጣቱን ፕሬዝዳንት ኬኔዲን የገደላቸው ሴአይኤ ራሱ ነው፤ ለዚያም ነው ገዳያቸው ነው የተባለውን ሰው ፈጥነው የገደሉት ብለው ያምናሉ።
ሲአይኤ ግን "የኔ እጅ የለበትም!" ይላል።
ገዳያቸው ነው የተባለው ኦስዋልድ በሜክሲኮ አገር ከኬጂቢ ሰላይ ጋር ተገናኝቶ እንደነበር ወደ በኋላ የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
የመጀመርያው የሮማን ካቶሊክ እምነት ተከታይ ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ በጊዜያቸው ገናና የነበሩ 35ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ከመሆናቸውም ባሻገር በንግግር አዋቂነታቸው ይደነቃሉ።
ከንግግራቸው አንዳንዶቹ ዛሬም ድረስ እንደ ጥቅስ ይወሳሉ፤ ከነዚህም መሀል ‘አገሬ ለኔ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን እኔ ለአገሬ ምን አደረኩላት ብለን እንጠይቅ’ የሚለው የበዓለ ሲመት ንግግራቸው በይበልጥ ይታወሳል።
***
እንደምታውቁት የፕሬዝዳንት ኬኔዲን ግድያ የተመለከተ የምርመራ ዶሴ ከ60 ዓመት በኋላ ይፋ ሆኗል።
ይህ ዶሴ ለሕዝብ ይፋ እየሆነ ያለው ከ60 ዓመታት ጥብቅ ምሥጢርነት በኋላ ነው።
ብዛቱ ከ10ሺህ በላይ ይሆናል የተባለው ይህ ሰነድ ይፋ እንዲሆን የወሰኑት ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ናቸው።
ይሁንና አንዳንድ ሰነዶች አሁንም በምሥጢር የሚቆዩ ይኖራሉ። ይህም ለአንዳንድ ሰዎች ደኀንነት ሲባል ነው።
ምንም እንኳ የጆን ኤፍ ኬኔዲ ግድያ ለዐሥርታት እያወዛገበ ቢቆይም በዚህ ሰነድ የሚገለጥ አንዳች ታላቅ ምሥጢር ይኖራል ተብሎ አይጠበቅም።
ይሁንና ዶሴው በፕሬዝዳንቱ ግድያ ዙርያ ጥናትና ምርምር ለሚያደርጉ ግን ልዩ ዕድል ነው ተብሏል።
የ1992 የአሜሪካ ሕግ ዶሴዎቹ በጥቅምት 2017 ለሕዝብ ይፋ እንዲደረጉ አስገዳጅ አድርጎ ነበር።
የአሜሪካ ብሔራዊ ቤተ መዛግብት ለሕዝብ ይፋ የማይደረጉት ሰነዶች ብዛት 515 ነው ብሏል።
ከጠቅላላው ሰነድ 2ሺህ 545 ሰነዶች ደግሞ ይፋ የሚሆኑት በከፊል ናቸው።
***
ታሪክን የኋሊት
ፕሬዚደንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ፤ ከኢትዮጵያዉ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጋር ጥሩ ግንኙነት ነበራቸዉ። በተለይ ጆን ኤፍ ኬኔዲ ከመገደላቸዉ ከአንድ ወር ቀደም ብሎ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አሜሪካንን መጎብኘታቸዉ ይነገራል።
ኢትዮጵያ በጆን ኤፍ ኬኔዲ፤ ዘመነ ሥልጣን ከዩኤስ አሜሪካ ጋር ጥሩ የወዳጅ ነት ግንኙነት እንደነበራት ቢታወቅም ጆኔፍ ኬኔዲ በተለይ ከኢትዮጵያዉ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንደነበራቸዉ ዘገባዎች ያመላክታሉ።
በደቡብ ቴክሳስ ዳላስ ከተማ፤ በተተኮሰባቸው ጥይት የተገደሉት ፕሬዚደንት ኬኔዲ ሥፍራ ቆሚያለሁ።
«ድል አባቷ ብዙ ነው" እንዲል ጆኔፍ ኬኔዲ ብዙ የታሪክ ምዕራፍ ለመሰነቅ ወደ ሙዚየሙ ገባሁ።
The joy and excitement of John Fitzgerald Kennedy's life belonged to all men.
So did the pain and sorrow of his death.
When he died on November 22, 1963, shock and agony touched human conscience throughout the world. In Dallas, Texas, there was a special sorrow.
The young President died in Dallas. The death bullets were fired 200 yards west of this site.
by Philip Johnson, This memorial, designed by was erected by the people by the people of Dallas. Thousands of citizens contributed support, money and effort.
It is not a memorial to the pain and sorrow of death, but stands as a permanent tribute to the joy and excitement of one man's life.
Pohn Fitzgerald Kennedy's life.
#ethiopia | በደቡብ ቴክሳስ ዳላስ ከተማ፤ በተተኮሰባቸው ጥይት የተገደሉት ፕሬዚደንት ኬኔዲ ሥፍራ ቆሚያለሁ።
የቀድሞው ዝነኛና ተወዳጁ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ በቴክሳስ ግዛት፣ ዳላስ ከተማ፣ በክፍት መኪና፤ በጉብኝት ሳሉ ነበር እኤአ በኅዳር 22፣ 1963 ቀትር ላይ በደቡብ ቴክሳስ ዳላስ ከተማ፤ በተተኮሰባቸው ጥይት የተገደሉት። ፕሬዚደንት ኬኔዲ ስልጣን ላይ ከወጡ ሦስተኛ ዓመታቸን ሊይዙ ትንሽ ወራት ይቀራቸው ነበር።
ከዚያች ቅጽበት ጀምሮ ሰውየውን ( ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ ) ማን ገደላቸው? ... ለምን ተገደሉ? ... በሚለው ዙርያ ሺህ ምርመራዎች ተደርገዋል።
እነዚህ የምርመራ ሂደቱን የያዙ ዶሴዎችም በምሥጢር ሲከማቹ ነው የኖሩት።
የ1964 የእውነት አፈላላጊው ‘ዋረን ኮሚሽን’ ፕሬዝዳንት ኬኔዲ የተገደሉት ሊ ሐርቬይ ኦስዋልድ በተባለ ግለሰብ ነው ብሎ ነበር።
ሊ ሐርቬይ ቀደም ሲል በሶቭየት ኅብረት ለአጭር ጊዜ የኖረ አሜሪካዊ ሲሆን ድርጊቱን የፈጸመውም በግሉ ነው ተብሎ ነበር።
በቁጥጥር ሥር በዋለ በሁለተኛው ቀን ግን ብዙም ግልጽ ባልሆነ መንገድ በዳላስ ፖሊስ ምድር ቤት ውስጥ ተገድሏል።
ይሁንና የኬኔዲ አገዳደል፣ ገዳያቸው ነበር የተባለው ሰው በፖሊስ ምድር ቤት መገደል ምሥጢርና ተያያዥ ጉዳዮች ለዐሥርታት ለብዙ መላምቶች ክፍት ሆኖ ቆይቷል።
የሴራ ፖለቲካ ተንታኞች ደግሞ ግድያውንና ግድያውን ተከትሎ የሆነውን ነገር ሁሉ የተለያዩ ትርጉም ሲሰጡት ኖረዋል። ዛሬም ድረስ ...
አንዳንዶች ወጣቱን ፕሬዝዳንት ኬኔዲን የገደላቸው ሴአይኤ ራሱ ነው፤ ለዚያም ነው ገዳያቸው ነው የተባለውን ሰው ፈጥነው የገደሉት ብለው ያምናሉ።
ሲአይኤ ግን "የኔ እጅ የለበትም!" ይላል።
ገዳያቸው ነው የተባለው ኦስዋልድ በሜክሲኮ አገር ከኬጂቢ ሰላይ ጋር ተገናኝቶ እንደነበር ወደ በኋላ የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
የመጀመርያው የሮማን ካቶሊክ እምነት ተከታይ ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ በጊዜያቸው ገናና የነበሩ 35ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ከመሆናቸውም ባሻገር በንግግር አዋቂነታቸው ይደነቃሉ።
ከንግግራቸው አንዳንዶቹ ዛሬም ድረስ እንደ ጥቅስ ይወሳሉ፤ ከነዚህም መሀል ‘አገሬ ለኔ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን እኔ ለአገሬ ምን አደረኩላት ብለን እንጠይቅ’ የሚለው የበዓለ ሲመት ንግግራቸው በይበልጥ ይታወሳል።
***
እንደምታውቁት የፕሬዝዳንት ኬኔዲን ግድያ የተመለከተ የምርመራ ዶሴ ከ60 ዓመት በኋላ ይፋ ሆኗል።
ይህ ዶሴ ለሕዝብ ይፋ እየሆነ ያለው ከ60 ዓመታት ጥብቅ ምሥጢርነት በኋላ ነው።
ብዛቱ ከ10ሺህ በላይ ይሆናል የተባለው ይህ ሰነድ ይፋ እንዲሆን የወሰኑት ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ናቸው።
ይሁንና አንዳንድ ሰነዶች አሁንም በምሥጢር የሚቆዩ ይኖራሉ። ይህም ለአንዳንድ ሰዎች ደኀንነት ሲባል ነው።
ምንም እንኳ የጆን ኤፍ ኬኔዲ ግድያ ለዐሥርታት እያወዛገበ ቢቆይም በዚህ ሰነድ የሚገለጥ አንዳች ታላቅ ምሥጢር ይኖራል ተብሎ አይጠበቅም።
ይሁንና ዶሴው በፕሬዝዳንቱ ግድያ ዙርያ ጥናትና ምርምር ለሚያደርጉ ግን ልዩ ዕድል ነው ተብሏል።
የ1992 የአሜሪካ ሕግ ዶሴዎቹ በጥቅምት 2017 ለሕዝብ ይፋ እንዲደረጉ አስገዳጅ አድርጎ ነበር።
የአሜሪካ ብሔራዊ ቤተ መዛግብት ለሕዝብ ይፋ የማይደረጉት ሰነዶች ብዛት 515 ነው ብሏል።
ከጠቅላላው ሰነድ 2ሺህ 545 ሰነዶች ደግሞ ይፋ የሚሆኑት በከፊል ናቸው።
***
ታሪክን የኋሊት
ፕሬዚደንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ፤ ከኢትዮጵያዉ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጋር ጥሩ ግንኙነት ነበራቸዉ። በተለይ ጆን ኤፍ ኬኔዲ ከመገደላቸዉ ከአንድ ወር ቀደም ብሎ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አሜሪካንን መጎብኘታቸዉ ይነገራል።
ኢትዮጵያ በጆን ኤፍ ኬኔዲ፤ ዘመነ ሥልጣን ከዩኤስ አሜሪካ ጋር ጥሩ የወዳጅ ነት ግንኙነት እንደነበራት ቢታወቅም ጆኔፍ ኬኔዲ በተለይ ከኢትዮጵያዉ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንደነበራቸዉ ዘገባዎች ያመላክታሉ።
በደቡብ ቴክሳስ ዳላስ ከተማ፤ በተተኮሰባቸው ጥይት የተገደሉት ፕሬዚደንት ኬኔዲ ሥፍራ ቆሚያለሁ።
«ድል አባቷ ብዙ ነው" እንዲል ጆኔፍ ኬኔዲ ብዙ የታሪክ ምዕራፍ ለመሰነቅ ወደ ሙዚየሙ ገባሁ።
The joy and excitement of John Fitzgerald Kennedy's life belonged to all men.
So did the pain and sorrow of his death.
When he died on November 22, 1963, shock and agony touched human conscience throughout the world. In Dallas, Texas, there was a special sorrow.
The young President died in Dallas. The death bullets were fired 200 yards west of this site.
by Philip Johnson, This memorial, designed by was erected by the people by the people of Dallas. Thousands of citizens contributed support, money and effort.
It is not a memorial to the pain and sorrow of death, but stands as a permanent tribute to the joy and excitement of one man's life.
Pohn Fitzgerald Kennedy's life.
10 months ago