1 day ago
ሰላም! እንደምን አደራችሁ?
ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚመራቸውን መንግሥት ለመምረጥ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 ቀን ከማለዳ ጀምሮ እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
ዜጎች በየአካባቢው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት÷ ኢትዮጵያውያን ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ለሀገረ መንግሥት ምስረታ ያላቸውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩበት ሆኖ አልፏል።
በሚሊየን የሚቆጠሩ መራጮች በነቂስ ወጥተው ዝናብና ጸሐይን እንዲሁም ከተለያዩ አካላት የሚነዙ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችንና ዛቻዎችን ሳያዳምጡ በረጃጅም ሰልፎች ተሰልፈው ውሳኔያቸውን አስተላልፈዋል።
በሕመም አልጋ ላይ የነበሩ ከሕመማቸው ጋር እየታገሉ፣ ሐዘን የገጠማቸውም ከሐዘናቸው ተነስተው በመውጣት ለነጋቸው የሚበጀውን ድምፅ የሰጡበት ዕለት ነው ግንቦት 24።
በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ ለመሳተፍ በሚያስችል ዕድሜ ላይ የሚገኙ ከ54 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተመዝግበው ከ10 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎችና 80 የግል ዕጩዎች በተወዳደሩበት ምርጫ ድምጻቸውን በመስጠት ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል።
የምርጫውን ግልጽነት፣ አሳታፊነትና ተዓማኒነት ከፍ ለማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን÷ ከእነዚህም መካከል ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ሚና ያላቸውና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፈቃድ ያገኙ 68 የመገናኛ ብዙኃን ተሰማርተዋል፤ ከእነዚህ ውስጥ 12ቱ የውጭ መገናኛ ብዙኃን ናቸው።
በተጨማሪም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድምፅ አሰጣጥና የውጤት ቆጠራ ሂደቱን በቅርበት ለመከታተል ከ250 ሺህ በላይ ተወካዮቻቸውን በየምርጫ ጣቢያዎቹ መድበዋል።
በሌላ በኩል የኬንያ ቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራውና 59 አባላትን የያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እንዲሁም 26 አባላትን ያሰማራው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመሰማራት ሂደቱን በንቃት ታዝበዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ÷ የምርጫው ድምፅ የመስጠት ሂደት በስኬት መጠናቀቁንና በየምርጫ ጣቢያዎቹ የምርጫ ውጤቶችን ለሕዝብ የመለጠፍ ሥራዎች በይፋ መከናወናቸውን አረጋግጠዋል።
ይህም ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል ለመወሰን መካሪና ገሳጭ እንደማያስፈልጋት በድጋሚ ያሳየበት ነው።
በድምፅ መስጫው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመራጩ ሕዝብ በላይ የተመራጮች ጉዳይና ኃላፊነት ይበልጥ እንደሚያሳስባቸው መግለጻቸው ይታወሳል።
በመሆኑም ሕዝብ ያሳየውን ፅኑ እምነትና የዴሞክራሲ ፍላጎት ሳይሸረሽር፣ በታማኝነትና በንጹሕ ልብ ማገልገል የነገው መንግሥት ቀዳሚ የቤት ሥራ እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንዖት ሰጥተዋል።
የሕዝቡን ሕይወት የሚነካና የሀገሪቱን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን እውነተኛ ለውጥ ማምጣት የሚቻለውም ተመራጮች የተጣለባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት በትክክል ተረድተው ሲሰናዱ ብቻ በመሆኑ የኢትዮጵያ ቀጣይ አምስት ዓመታት ጉዞ በዚሁ የተመራጮች የዝግጁነት ሚዛን ላይ የሚያርፍ ይሆናል።
ኢትዮጵያ መርጣለች፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!!
ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚመራቸውን መንግሥት ለመምረጥ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 ቀን ከማለዳ ጀምሮ እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
ዜጎች በየአካባቢው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት÷ ኢትዮጵያውያን ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ለሀገረ መንግሥት ምስረታ ያላቸውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩበት ሆኖ አልፏል።
በሚሊየን የሚቆጠሩ መራጮች በነቂስ ወጥተው ዝናብና ጸሐይን እንዲሁም ከተለያዩ አካላት የሚነዙ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችንና ዛቻዎችን ሳያዳምጡ በረጃጅም ሰልፎች ተሰልፈው ውሳኔያቸውን አስተላልፈዋል።
በሕመም አልጋ ላይ የነበሩ ከሕመማቸው ጋር እየታገሉ፣ ሐዘን የገጠማቸውም ከሐዘናቸው ተነስተው በመውጣት ለነጋቸው የሚበጀውን ድምፅ የሰጡበት ዕለት ነው ግንቦት 24።
በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ ለመሳተፍ በሚያስችል ዕድሜ ላይ የሚገኙ ከ54 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተመዝግበው ከ10 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎችና 80 የግል ዕጩዎች በተወዳደሩበት ምርጫ ድምጻቸውን በመስጠት ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል።
የምርጫውን ግልጽነት፣ አሳታፊነትና ተዓማኒነት ከፍ ለማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን÷ ከእነዚህም መካከል ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ሚና ያላቸውና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፈቃድ ያገኙ 68 የመገናኛ ብዙኃን ተሰማርተዋል፤ ከእነዚህ ውስጥ 12ቱ የውጭ መገናኛ ብዙኃን ናቸው።
በተጨማሪም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድምፅ አሰጣጥና የውጤት ቆጠራ ሂደቱን በቅርበት ለመከታተል ከ250 ሺህ በላይ ተወካዮቻቸውን በየምርጫ ጣቢያዎቹ መድበዋል።
በሌላ በኩል የኬንያ ቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራውና 59 አባላትን የያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እንዲሁም 26 አባላትን ያሰማራው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመሰማራት ሂደቱን በንቃት ታዝበዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ÷ የምርጫው ድምፅ የመስጠት ሂደት በስኬት መጠናቀቁንና በየምርጫ ጣቢያዎቹ የምርጫ ውጤቶችን ለሕዝብ የመለጠፍ ሥራዎች በይፋ መከናወናቸውን አረጋግጠዋል።
ይህም ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል ለመወሰን መካሪና ገሳጭ እንደማያስፈልጋት በድጋሚ ያሳየበት ነው።
በድምፅ መስጫው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመራጩ ሕዝብ በላይ የተመራጮች ጉዳይና ኃላፊነት ይበልጥ እንደሚያሳስባቸው መግለጻቸው ይታወሳል።
በመሆኑም ሕዝብ ያሳየውን ፅኑ እምነትና የዴሞክራሲ ፍላጎት ሳይሸረሽር፣ በታማኝነትና በንጹሕ ልብ ማገልገል የነገው መንግሥት ቀዳሚ የቤት ሥራ እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንዖት ሰጥተዋል።
የሕዝቡን ሕይወት የሚነካና የሀገሪቱን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን እውነተኛ ለውጥ ማምጣት የሚቻለውም ተመራጮች የተጣለባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት በትክክል ተረድተው ሲሰናዱ ብቻ በመሆኑ የኢትዮጵያ ቀጣይ አምስት ዓመታት ጉዞ በዚሁ የተመራጮች የዝግጁነት ሚዛን ላይ የሚያርፍ ይሆናል።
ኢትዮጵያ መርጣለች፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!!
2 days ago
የሕዝብ ጽናት፦ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የስኬት ምስጢር
*****************
በኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ተቋማት ግንባታና ተዓማኒነትን ለማረጋገጥ የተከናወነው ተግባር ተጨባጭ ፍሬ እያፈራ መሆኑን የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተግባር አሳይቷል።
በምርጫው ዕለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፁ እንዳይባክን እና ሉዓላዊ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ጽናት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት ሀገሩን ለማጽናት የከፈለው ታላቅ የዜግነት መስዋዕትነት ሆኖ ተመዝግቧል።
በምርጫው ዕለት ሕዝባችን ቁር ሳይበግረው ጎሕ ከመቅደዱ፣ የምርጫ ጣቢያዎችም ከመከፈታቸው በፊት በየምድብ ስፍራው በመድረስና ረጃጅም ሰልፎችን በመታገስ ጽናቱን አሳይቷል።
እናቶች፣ አባቶች፣ ወጣቶችና አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች የመራጭነት ካርዳቸውን በመያዝ በየምርጫ ጣቢያዎቻቸው በማለዳ ደርሰዋል።
ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀምና የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት ያደረጉት ኃላፊነት የተሞላበት እንቅስቃሴና ያሳዩት ጽናት እጅግ የሚያስደንቅ ነበር።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስምሪት የተሰጣቸው አስመራጮች፣ ታዛቢዎችና የጸጥታ አካላትም አስቀድመው በየምድብ ጣቢያዋቻቸው በመገኘት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ተወጥተዋል።
የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ምሽት 12 ሰዓት ላይ መጠናቀቅ የነበረበት ቢሆንም፣ በነበረው ከፍተኛ የመራጮች ቁጥርና የሂደት መጓተት ችግር ምክንያት በምርጫ ቦርድ ውሳኔ ሂደቱ እስከ እኩለ ሌሊትና ከዚያም በላይ እንዲራዘም ተደርጓል።
ይህን ተከትሎም ምርጫው በስኬት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህም ሀገራችን ማንኛውንም ታላቅ ሁነት በብቃት ማካሄድ እንደምትችል ዳግም ያረጋገጠችበት ሆኗል።
ይህም ሕዝባችን ምርጫ ተራ ሁነት ሳይሆን፣ የሀገርን እጣ ፈንታ መወሰኛ ታላቅ ዕድል መሆኑን በተግባር ያሳየበት ነው።
በአጠቃላይ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ያሳየው የፖለቲካ ብስለትና ጽናት፣ የሰላም እና የሀገር ወዳድነቱ መገለጫ ነው።
አዎ፣ ምርጫው ሕዝባችን ለነገዋ ኢትዮጵያ ጠንካራ የዴሞክራሲ መሠረት ለመጣል ያለውን የላቀ ፍላጎት በግልጽ ያሳየበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
በመሐመድ ፊጣሞ
#ኢትዮጵያ_መርጣለች #ኢትዮጵያ_አሸንፋለች
*****************
በኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ተቋማት ግንባታና ተዓማኒነትን ለማረጋገጥ የተከናወነው ተግባር ተጨባጭ ፍሬ እያፈራ መሆኑን የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በተግባር አሳይቷል።
በምርጫው ዕለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፁ እንዳይባክን እና ሉዓላዊ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ጽናት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት ሀገሩን ለማጽናት የከፈለው ታላቅ የዜግነት መስዋዕትነት ሆኖ ተመዝግቧል።
በምርጫው ዕለት ሕዝባችን ቁር ሳይበግረው ጎሕ ከመቅደዱ፣ የምርጫ ጣቢያዎችም ከመከፈታቸው በፊት በየምድብ ስፍራው በመድረስና ረጃጅም ሰልፎችን በመታገስ ጽናቱን አሳይቷል።
እናቶች፣ አባቶች፣ ወጣቶችና አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች የመራጭነት ካርዳቸውን በመያዝ በየምርጫ ጣቢያዎቻቸው በማለዳ ደርሰዋል።
ዜጎች ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ለመጠቀምና የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት ያደረጉት ኃላፊነት የተሞላበት እንቅስቃሴና ያሳዩት ጽናት እጅግ የሚያስደንቅ ነበር።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስምሪት የተሰጣቸው አስመራጮች፣ ታዛቢዎችና የጸጥታ አካላትም አስቀድመው በየምድብ ጣቢያዋቻቸው በመገኘት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ተወጥተዋል።
የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ምሽት 12 ሰዓት ላይ መጠናቀቅ የነበረበት ቢሆንም፣ በነበረው ከፍተኛ የመራጮች ቁጥርና የሂደት መጓተት ችግር ምክንያት በምርጫ ቦርድ ውሳኔ ሂደቱ እስከ እኩለ ሌሊትና ከዚያም በላይ እንዲራዘም ተደርጓል።
ይህን ተከትሎም ምርጫው በስኬት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህም ሀገራችን ማንኛውንም ታላቅ ሁነት በብቃት ማካሄድ እንደምትችል ዳግም ያረጋገጠችበት ሆኗል።
ይህም ሕዝባችን ምርጫ ተራ ሁነት ሳይሆን፣ የሀገርን እጣ ፈንታ መወሰኛ ታላቅ ዕድል መሆኑን በተግባር ያሳየበት ነው።
በአጠቃላይ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕዝባችን ያሳየው የፖለቲካ ብስለትና ጽናት፣ የሰላም እና የሀገር ወዳድነቱ መገለጫ ነው።
አዎ፣ ምርጫው ሕዝባችን ለነገዋ ኢትዮጵያ ጠንካራ የዴሞክራሲ መሠረት ለመጣል ያለውን የላቀ ፍላጎት በግልጽ ያሳየበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
በመሐመድ ፊጣሞ
#ኢትዮጵያ_መርጣለች #ኢትዮጵያ_አሸንፋለች
2 days ago
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ በሰጡት መግለጫ ምን ምን ጉዳዮችን አነሱ?
**********************
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፣ ከድምፅ መስጫ ቀን በኋላ ያለውን አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ሁኔታና ቀጣይ ሥራዎችን አስመልክተው በሰጡት ማጠቃለያ መግለጫ በርካታ ዋና ዋና ጉዳዮችን አንስተዋል፡፡ ሰብሳቢዋ በመግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
የድምፅ አሰጣጥ እና የቆጠራ ሂደት ወቅታዊ ሁኔታ፦ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን የተከናወነው የድምፅ መስጠት ሂደት በአብዛኛው በጥሩ ሁኔታ መከናወኑን የገለጹት ሰብሳቢዋ፣ የተወሰኑ ክልሎች በሰዓቱ አጠናቀው ወዲያውኑ ወደ ቆጠራ መግባታቸውንና አንዳንዶቹ ደግሞ ቆጠራውን አሳድረው ማከናወናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በተለየ ሁኔታ በአዲስ አበባ በነበረው ረጅም ሰልፍ ምክንያት ቦርዱ እስከ ሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ የጊዜ ማራዘሚያ ማድረጉንና በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ እንዲሁም በሲዳማ፣ በጋምቤላ፣ በአማራ እና በሶማሌ ክልሎች የሚገኙ የተወሰኑ ምርጫ ጣቢያዎች አሁንም በድምፅ ቆጠራ ሥራ ላይ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡
የመዘግየት ችግሮች እና የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች፦ በአዲስ አበባ የተስተዋለውን የሰልፍ መርዘምና የመዘግየት ችግር ለመፍታት ቦርዱ በርካታ ከፍተኛ ባለሙያዎችንና ኤክስፐርቶችን ወደ ጣቢያዎች መድቦ እንደነበር ሰብሳቢዋ አስታውቀዋል፡፡
ለመዘግየቱ እንደ ምክንያት ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች በመራጮች መዝገብ ላይ ስም የመፈለግ ሂደት መርዘም እና በአንዳንድ ጣቢያዎች የዕጩዎች ቁጥር እስከ 123 መድረሱ መራጮች በምስጢር ድምፅ መስጫ ክፍል ውስጥ የሚወስዱትን ደቂቃ ማርዘሙን ነው፡፡
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ቦርዱ ተጨማሪ የድምፅ መስጫ ሳጥኖችንና ቡዞችን ወደ ጣቢያዎች ልኮ መፍትሔ ለመስጠት መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ቅሬታዎችን ማስተናገድና የተወሰዱ የቅጣት እርምጃዎች፦ ቦርዱ በሕግ ክፍል፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች የሥራ ክፍል፣ በ6412 የጥሪ ማዕከልና ከታዛቢዎች በሚደርሱት ጥቆማዎች መሠረት የርምትና የማጣራት እርምጃዎችን ሲወስድ መቆየቱን ሜላትወርቅ ኃይሉ ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ አንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች መግባት የሌለባቸው ሰዎች ስለመታየታቸው የቀረቡ ጥቆማዎችን ቦርዱ በሞኒተሪንግ ቡድን አጣርቶ እውነት ሆነው በተገኙት ላይ እርምጃ መውሰዱንና ሕግና ደንብ ጥሰው የተገኙ የምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችን ማሰናበቱን አረጋግጠዋል፡፡
የውጤት አሰጣጥ እና የማረጋገጥ ቀጣይ ሥራዎች፦ በአሁኑ ወቅት የምርጫ ውጤታቸው በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ተደምሮ ያለቀላቸው ውጤቶች በየጣቢያዎቹ ተለጥፈው ለሕዝብ ይፋ መደረጋቸውን የጠቀሱት ሰብሳቢዋ፣ ቀጥሎም ውጤቶቹ ወደ ምርጫ ክልል ሄደው የማዳመር ሥራ እንደሚሠራ አስረድተዋል፡፡
በመጨረሻም ውጤቶቹ ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት የማረጋገጫ ማዕከል ከመጡ በኋላ፣ ከተመዘገበው የመራጭ ቁጥር አንጻር ዋጋ ያላቸው እና የሌላቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ተለይተው የማረጋገጥ ሥራው በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ቦርዱ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡
#ኢትዮጵያ_መርጣለች #ኢትዮጵያ_አሸንፋለች
**********************
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፣ ከድምፅ መስጫ ቀን በኋላ ያለውን አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ሁኔታና ቀጣይ ሥራዎችን አስመልክተው በሰጡት ማጠቃለያ መግለጫ በርካታ ዋና ዋና ጉዳዮችን አንስተዋል፡፡ ሰብሳቢዋ በመግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
የድምፅ አሰጣጥ እና የቆጠራ ሂደት ወቅታዊ ሁኔታ፦ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን የተከናወነው የድምፅ መስጠት ሂደት በአብዛኛው በጥሩ ሁኔታ መከናወኑን የገለጹት ሰብሳቢዋ፣ የተወሰኑ ክልሎች በሰዓቱ አጠናቀው ወዲያውኑ ወደ ቆጠራ መግባታቸውንና አንዳንዶቹ ደግሞ ቆጠራውን አሳድረው ማከናወናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በተለየ ሁኔታ በአዲስ አበባ በነበረው ረጅም ሰልፍ ምክንያት ቦርዱ እስከ ሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ የጊዜ ማራዘሚያ ማድረጉንና በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ እንዲሁም በሲዳማ፣ በጋምቤላ፣ በአማራ እና በሶማሌ ክልሎች የሚገኙ የተወሰኑ ምርጫ ጣቢያዎች አሁንም በድምፅ ቆጠራ ሥራ ላይ እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡
የመዘግየት ችግሮች እና የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች፦ በአዲስ አበባ የተስተዋለውን የሰልፍ መርዘምና የመዘግየት ችግር ለመፍታት ቦርዱ በርካታ ከፍተኛ ባለሙያዎችንና ኤክስፐርቶችን ወደ ጣቢያዎች መድቦ እንደነበር ሰብሳቢዋ አስታውቀዋል፡፡
ለመዘግየቱ እንደ ምክንያት ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች በመራጮች መዝገብ ላይ ስም የመፈለግ ሂደት መርዘም እና በአንዳንድ ጣቢያዎች የዕጩዎች ቁጥር እስከ 123 መድረሱ መራጮች በምስጢር ድምፅ መስጫ ክፍል ውስጥ የሚወስዱትን ደቂቃ ማርዘሙን ነው፡፡
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ቦርዱ ተጨማሪ የድምፅ መስጫ ሳጥኖችንና ቡዞችን ወደ ጣቢያዎች ልኮ መፍትሔ ለመስጠት መቻሉን ገልጸዋል፡፡
ቅሬታዎችን ማስተናገድና የተወሰዱ የቅጣት እርምጃዎች፦ ቦርዱ በሕግ ክፍል፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች የሥራ ክፍል፣ በ6412 የጥሪ ማዕከልና ከታዛቢዎች በሚደርሱት ጥቆማዎች መሠረት የርምትና የማጣራት እርምጃዎችን ሲወስድ መቆየቱን ሜላትወርቅ ኃይሉ ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ አንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች መግባት የሌለባቸው ሰዎች ስለመታየታቸው የቀረቡ ጥቆማዎችን ቦርዱ በሞኒተሪንግ ቡድን አጣርቶ እውነት ሆነው በተገኙት ላይ እርምጃ መውሰዱንና ሕግና ደንብ ጥሰው የተገኙ የምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችን ማሰናበቱን አረጋግጠዋል፡፡
የውጤት አሰጣጥ እና የማረጋገጥ ቀጣይ ሥራዎች፦ በአሁኑ ወቅት የምርጫ ውጤታቸው በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ተደምሮ ያለቀላቸው ውጤቶች በየጣቢያዎቹ ተለጥፈው ለሕዝብ ይፋ መደረጋቸውን የጠቀሱት ሰብሳቢዋ፣ ቀጥሎም ውጤቶቹ ወደ ምርጫ ክልል ሄደው የማዳመር ሥራ እንደሚሠራ አስረድተዋል፡፡
በመጨረሻም ውጤቶቹ ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት የማረጋገጫ ማዕከል ከመጡ በኋላ፣ ከተመዘገበው የመራጭ ቁጥር አንጻር ዋጋ ያላቸው እና የሌላቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ተለይተው የማረጋገጥ ሥራው በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ቦርዱ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡
#ኢትዮጵያ_መርጣለች #ኢትዮጵያ_አሸንፋለች
2 days ago
ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡
ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡
ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
2 days ago
ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች! - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
***********************
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችውን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት። ለሀገራቸው የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች። ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል። ዛሬ የተደገመውም ይኸው ነው።
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች። ለዚህ ደግሞ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር።
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል። እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈው ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው።
ምርጫው እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተው ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም። ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል። ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች።
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃው ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫውን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች።
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ግንቦት 25 2018፣ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ
#ebc #ethiopia #gcs
***********************
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችውን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት። ለሀገራቸው የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች። ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል። ዛሬ የተደገመውም ይኸው ነው።
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች። ለዚህ ደግሞ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር።
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል። እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈው ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው።
ምርጫው እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተው ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም። ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል። ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች።
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃው ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫውን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች።
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ግንቦት 25 2018፣ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ
#ebc #ethiopia #gcs
9 months ago
በአባይ ወንዝ ላይ የተደረገው የውሃ "ጦርነት" አብቅቷል።ኢትዮጵያ አሸንፋለች ። የግብፅ እጅ ከታሰረ የሱዳንም ተሰብሯል
#ethiopia | ሱዳናዊው ፀሀፊ አልፋድል ኢብራሂም ህዳሴ ግድብን አስመልክቶ በአረብ ዊክሊ ላይ ከፃፈው ፅሁፍ የተወሰደ።
ፀሀፊው ህዳሴ ግድብ ላይ ግብፅ እንደተሸነፈች ቢገልፅም የኢትዮጵያን ወደብ መፈለግ በአዎንታዊ መልኩ መሳል አልፈለገም።
ለማንኛውም ፅሁፉ ይሄን ይመስላል;
ለ10 ዓመታት ያህል በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ትልቁ የውሃ ግጭት ሊሆን ይችላል ተብሎ የብዙዎችን ትኩረት ስቦ ነበር። ታሪኩ ቀጥተኛ እና ሀይለኛ ነበር፡ ኢትዮጵያ እያደገች ያለችው የላይኛው ተፋሰስ ሀይል ግብጽን፣ ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የታችኛው ተፋሰስ የበላይ ተንሳፋፊ፣ የሚያንቀውን እና በመጨረሻም ጦርነት የሚያስነሳ ትልቅ ግድብ እየገነባች ነበር።
የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የ5 ቢሊዮን ዶላር ግድብን “በጥቁር ዘር ታሪክ ትልቁ ስኬት” ሲሉ አሞካሽተዋል፣ ትረካው ጷግሜ 4 ይፋዊ ፍጻሜውን አግኝቷል።
አንዴ በግብጽ እጅ የነበሩት የሥልጣን ጥንታዊ ማንሻዎች ዝገው ፈራርሰዋል። ዓለም አቀፍ ሽምግልና ጠፍቷል፣ የታችኛው ተፋሰስ ጥምረት ተበላሽቷል፣ እናም አዲስና ውስብስብ ጨዋታ አሁን በናይል ሸለቆ እየተካሄደ ነው—የዚህ ጨዋታ ሽልማቱ ራሱ ቦርዱ እንጂ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አይደለም።
የግብጽ ወታደራዊ አማራጭ ሙሉ በሙሉ መቋጨት በዚህ አዲስ እውነታ ውስጥ በጣም አስፈላጊው አካል ነው። ቀደም ሲል ዜናዎችን ሲቆጣጠር የነበረው የጦርነት ቅስቀሳ አሁን ባዶ ይመስላል። አንድ ሰው የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ2020 ግብጽ በመጨረሻ "ያንን ግድብ እንደምትደመሰስ" የሰጡትን ግልጽ ትንበያ ያስታውሳል። በወቅቱ አስተያየቱ በካይሮ ውስጥ እየታሰበበት የነበረውን አዋጭ፣ ምንም እንኳን ሥር ነቀል፣ የድርጊት አካሄድ ይወክል ነበር።
ያ አማራጭ አሁን ከፖለቲካዊ እና ወታደራዊ እይታ አንጻር ሊታሰብ የማይችል ነው። ግብፅ ሊፈቱ የሚገቡ ብዙ ጉዳዮች አሉባት። የእስራኤል ጥቃት በኳታር ላይ ከተሰነዘረ በኋላ ይበልጥ የካይሮ ችግር በሆነው በጋዛ ያለው አሰቃቂ ግጭት እና ከዚህም የመነጨው ሰብአዊ ጥፋት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የደህንነት ሀብቶቿን አሟጦታል።
ግብፅ ለጋዛ ወሳኝ አስታራቂ፣ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ሰዎች የስደተኞች መጠለያ እና ሰፊ ክልላዊ ሁከትን የምትከላከል እንደመሆኗ መጠን በደቡባዊ ድንበሯ ላይ ወታደራዊ ጀብዱ ለመፈጸም ፍላጎት የላትም። ካይሮ ከ125 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያን የመዋጋት አደጋን መውሰድ አትችልም ።
ይህ ስልታዊ ወደኋላ መመለስ የምስረታው ውጤት እና ሁኔታው ያመጣው ለውጥ ነው። የግብፅ ባለስልጣናት የኢትዮጵያን "አንድ ወገንተኝነት የተሞላበት እርምጃ" ማውገዝ እና ስለ "ህልውና አደጋ" አስከፊ ማስጠንቀቂያዎችን ማስተላለፋቸውን ሲቀጥሉ፣ የግብጽ ዕቅድ አውጪዎች ግን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሊቀበል የሚችል የወደፊት ሁኔታ በድብቅ እየፈጠሩ ነው። ለዚህም የግብጽ ከፍተኛ ጨዋማ ውሃ በማጥለል ንፁህ ውሃ ማቅረብ ኢንቨስትመንት ማረጋገጫ ሆኖ ያገለግላል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ማድቡሊ በቀጣዮቹ ስድስት ዓመታት በየቀኑ 10 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የተጣራ ውሃ ለማምረት ያለመውን ታላቅ እቅድ አስታውቀዋል። ከ100 በላይ የጨው ማስወገጃ ተቋማት ወደ ስራ የገቡ ሲሆን ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ሌሎችም ለመገንባት ታቅዷል። ግብፅ በናይል ወንዝ ላይ የነበራትን ጥገኝነት በመቀነስ የውሃ ደህንነቷን እንደ አዲስ እያሻሻለች ነው። አብዛኛውን የውሃ ድርሻ የሰጧት የ1929 እና 1959 ስምምነቶች ይደግፉት የነበረው የድሮው የውሃ ፖለቲካዊ ስርዓት ከጥቅም ውጪ መሆኑ በተዘዋዋሪ መንገድ ታውቋል። ካይሮ ግድቡን ከማፍረስ ይልቅ በግድቡ ዙሪያ እቅድ እያወጣች ነው።
ግብፅ እጇ ከታሰረች የሱዳን እጅም ተሰብሯል። ቀደም ሲል የግብጽ ዋና እና የውሃ ተጋሪ ሀገር የነበረችው ሱዳን ከፈረንጆቹ ከሚያዚያ 2023 ጀምሮ በአሰቃቂ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ገብታለች።
በአካባቢው የውክልና ግጭቶች መፋለሚያ በመሆኗ፣ የሀገሪቱ ዲፕሎማሲያዊ ተጽእኖ ቀንሷል። በዋና ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ደጋፊዋ በግብፅ ላይ የህልውና ጥገኛ በመሆኗ፣ በፖርት ሱዳን የሚገኘው በሱዳን ጦር ኃይሎች (ኤስ.ኤ.ኤፍ.) የሚመራው መንግስት በይፋ የካይሮን የፀረ-ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አቋም ለመደገፍ ተገድዷል።
ይሁን እንጂ፣ ያለው እውነታ እጅግ አሳዛኝ እና ውስብስብ ነው። በህዳር 2015፣ ከእርስ በርስ ጦርነቱ በፊት፣ ነገር ግን አገሪቷ ከ2011ቱ አብዮት በኋላ እየፈረሰች ባለበት ወቅት፣ አልጀዚራ ይፋ ባደረገው ሚስጥራዊ ሰነድ መሰረት፣ ካርቱም እና ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሙሌትና አሰራር በተመለከተ የቴክኒክ ስምምነት ተፈራርመዋል።
በሱዳን ድንበር ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ግድቡ በመጨረሻ እንደሚጠናቀቅና ሱዳንም ለራሷ ግድቦች የውሃ ፍሰትን ለመቆጣጠርና የኤሌክትሪክ አቅርቦቷን ለማረጋገጥ ከአዲስ አበባ ጋር አብሮ መስራት እንዳለባት በስውር አምናለች።
ይህ ጥገኝነት ዛሬ ይበልጥ ጎልቶ ይታያል። ካይሮ የሱዳንን ጦር ኃይሎች እየደገፈች ባለበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ ለሱዳን የኃይል አቅርቦት እየሰጠች ነው፣ ይህም ለሶስት አመታት ያልተከፈለ እና ከ90 ሚሊዮን ዶላር በላይ የደረሰ ዕዳ እየተጠራቀመ ነው። በዚህም ምክንያት ሱዳን በንግግር ደረጃ ግብጽ የምትደግፍ ስትሆን በተግባር ግን በኢትዮጵያ ላይ ጥገኛ ሆናለች። የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ግንባር በመበተኑ ምክንያት ግብጽ አሁን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ብቸኛ ሆናለች።
በተጨማሪም የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ሌላው ወሳኝ ለውጥ አሳይተዋል። በአሜሪካ እና በአለም ባንክ የሚመራው ድርድር ከከሸፈ በኋላ እንደ ዋና አስታራቂ ስትታይ የነበረችው የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አሁን ባለድርሻ ሆናለች። በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ከሆኑት ከሼክ ታህኖን ቢን ዛይድ ጋር ግንኙነት ያለው አንድ ድርጅት በቅርቡ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር የተፈራረመው የኃይል ግዢ ስምምነት አቡ ዳቢ አዲሱን ነባራዊ ሁኔታ መቀበል ብቻ ሳይሆን በንቃት እየተጠቀመችበት እንደሆነ ግልጽ ማሳያ ነው።
ግብፅ ከቀድሞ አጋሮቿ ወይም አሸማጋዮዎች ጋር መተማመን ስላልቻለች አዲስ ጥምረት ለመፍጠር ተገድዳለች። ለዚህም አጋጣሚውን የፈጠረው የኢትዮጵያ በ2024 ከሶማሊላንድ ጋር ያደረገችው የባህር በር ስምምነት ነው። ይህ ስምምነት የፌደራል መንግስቱን ያስቆጣና ያለፈቃድ የተደረገ በመሆኑ ግብጽ ይህን እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር ከሞቃዲሾ ጋር የደህንነት ስምምነት በፍጥነት በመፈረም፣ አዲሱን የኤርትራ-ግብጽ-ሶማሊያ የይዞታ ዘንግን መሰረተች።
ለኢትዮጵያ አወዛጋቢ የባህር በር ስምምነት ከሶማሊላንድ ጋር በምላሽ፣ የሶስቱ ሀገራት ጥምረት ለየአባላቱ ግልጽ ጥቅሞችን አስገኝቷል፡- ግብፅ በኢትዮጵያ ምስራቃዊ ድንበር ላይ ስትራቴጂካዊ ቦታ አገኘች፣ በራሷ ተነጥላ የነበረችው ኤርትራ በአብይ የአሰብ ወደብ ከተማን በተመለከተ ካላት ጠበኛ እቅድ ጋር ጠንካራ አጋር አገኘች፤ ሶማሊያ ደግሞ ከአል-ሻባብ ጋር በሚደረገው ውጊያ ተጨማሪ ድጋፍ እና ግዛቷ እንዳይከፋፈል የፀጥታ ዋስትና አገኘች ሲል ፊደል ፖስት ገልጿል።
#ethiopia | ሱዳናዊው ፀሀፊ አልፋድል ኢብራሂም ህዳሴ ግድብን አስመልክቶ በአረብ ዊክሊ ላይ ከፃፈው ፅሁፍ የተወሰደ።
ፀሀፊው ህዳሴ ግድብ ላይ ግብፅ እንደተሸነፈች ቢገልፅም የኢትዮጵያን ወደብ መፈለግ በአዎንታዊ መልኩ መሳል አልፈለገም።
ለማንኛውም ፅሁፉ ይሄን ይመስላል;
ለ10 ዓመታት ያህል በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ትልቁ የውሃ ግጭት ሊሆን ይችላል ተብሎ የብዙዎችን ትኩረት ስቦ ነበር። ታሪኩ ቀጥተኛ እና ሀይለኛ ነበር፡ ኢትዮጵያ እያደገች ያለችው የላይኛው ተፋሰስ ሀይል ግብጽን፣ ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የታችኛው ተፋሰስ የበላይ ተንሳፋፊ፣ የሚያንቀውን እና በመጨረሻም ጦርነት የሚያስነሳ ትልቅ ግድብ እየገነባች ነበር።
የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የ5 ቢሊዮን ዶላር ግድብን “በጥቁር ዘር ታሪክ ትልቁ ስኬት” ሲሉ አሞካሽተዋል፣ ትረካው ጷግሜ 4 ይፋዊ ፍጻሜውን አግኝቷል።
አንዴ በግብጽ እጅ የነበሩት የሥልጣን ጥንታዊ ማንሻዎች ዝገው ፈራርሰዋል። ዓለም አቀፍ ሽምግልና ጠፍቷል፣ የታችኛው ተፋሰስ ጥምረት ተበላሽቷል፣ እናም አዲስና ውስብስብ ጨዋታ አሁን በናይል ሸለቆ እየተካሄደ ነው—የዚህ ጨዋታ ሽልማቱ ራሱ ቦርዱ እንጂ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አይደለም።
የግብጽ ወታደራዊ አማራጭ ሙሉ በሙሉ መቋጨት በዚህ አዲስ እውነታ ውስጥ በጣም አስፈላጊው አካል ነው። ቀደም ሲል ዜናዎችን ሲቆጣጠር የነበረው የጦርነት ቅስቀሳ አሁን ባዶ ይመስላል። አንድ ሰው የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ2020 ግብጽ በመጨረሻ "ያንን ግድብ እንደምትደመሰስ" የሰጡትን ግልጽ ትንበያ ያስታውሳል። በወቅቱ አስተያየቱ በካይሮ ውስጥ እየታሰበበት የነበረውን አዋጭ፣ ምንም እንኳን ሥር ነቀል፣ የድርጊት አካሄድ ይወክል ነበር።
ያ አማራጭ አሁን ከፖለቲካዊ እና ወታደራዊ እይታ አንጻር ሊታሰብ የማይችል ነው። ግብፅ ሊፈቱ የሚገቡ ብዙ ጉዳዮች አሉባት። የእስራኤል ጥቃት በኳታር ላይ ከተሰነዘረ በኋላ ይበልጥ የካይሮ ችግር በሆነው በጋዛ ያለው አሰቃቂ ግጭት እና ከዚህም የመነጨው ሰብአዊ ጥፋት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የደህንነት ሀብቶቿን አሟጦታል።
ግብፅ ለጋዛ ወሳኝ አስታራቂ፣ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ሰዎች የስደተኞች መጠለያ እና ሰፊ ክልላዊ ሁከትን የምትከላከል እንደመሆኗ መጠን በደቡባዊ ድንበሯ ላይ ወታደራዊ ጀብዱ ለመፈጸም ፍላጎት የላትም። ካይሮ ከ125 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያን የመዋጋት አደጋን መውሰድ አትችልም ።
ይህ ስልታዊ ወደኋላ መመለስ የምስረታው ውጤት እና ሁኔታው ያመጣው ለውጥ ነው። የግብፅ ባለስልጣናት የኢትዮጵያን "አንድ ወገንተኝነት የተሞላበት እርምጃ" ማውገዝ እና ስለ "ህልውና አደጋ" አስከፊ ማስጠንቀቂያዎችን ማስተላለፋቸውን ሲቀጥሉ፣ የግብጽ ዕቅድ አውጪዎች ግን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሊቀበል የሚችል የወደፊት ሁኔታ በድብቅ እየፈጠሩ ነው። ለዚህም የግብጽ ከፍተኛ ጨዋማ ውሃ በማጥለል ንፁህ ውሃ ማቅረብ ኢንቨስትመንት ማረጋገጫ ሆኖ ያገለግላል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ማድቡሊ በቀጣዮቹ ስድስት ዓመታት በየቀኑ 10 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የተጣራ ውሃ ለማምረት ያለመውን ታላቅ እቅድ አስታውቀዋል። ከ100 በላይ የጨው ማስወገጃ ተቋማት ወደ ስራ የገቡ ሲሆን ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ሌሎችም ለመገንባት ታቅዷል። ግብፅ በናይል ወንዝ ላይ የነበራትን ጥገኝነት በመቀነስ የውሃ ደህንነቷን እንደ አዲስ እያሻሻለች ነው። አብዛኛውን የውሃ ድርሻ የሰጧት የ1929 እና 1959 ስምምነቶች ይደግፉት የነበረው የድሮው የውሃ ፖለቲካዊ ስርዓት ከጥቅም ውጪ መሆኑ በተዘዋዋሪ መንገድ ታውቋል። ካይሮ ግድቡን ከማፍረስ ይልቅ በግድቡ ዙሪያ እቅድ እያወጣች ነው።
ግብፅ እጇ ከታሰረች የሱዳን እጅም ተሰብሯል። ቀደም ሲል የግብጽ ዋና እና የውሃ ተጋሪ ሀገር የነበረችው ሱዳን ከፈረንጆቹ ከሚያዚያ 2023 ጀምሮ በአሰቃቂ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ገብታለች።
በአካባቢው የውክልና ግጭቶች መፋለሚያ በመሆኗ፣ የሀገሪቱ ዲፕሎማሲያዊ ተጽእኖ ቀንሷል። በዋና ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ደጋፊዋ በግብፅ ላይ የህልውና ጥገኛ በመሆኗ፣ በፖርት ሱዳን የሚገኘው በሱዳን ጦር ኃይሎች (ኤስ.ኤ.ኤፍ.) የሚመራው መንግስት በይፋ የካይሮን የፀረ-ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አቋም ለመደገፍ ተገድዷል።
ይሁን እንጂ፣ ያለው እውነታ እጅግ አሳዛኝ እና ውስብስብ ነው። በህዳር 2015፣ ከእርስ በርስ ጦርነቱ በፊት፣ ነገር ግን አገሪቷ ከ2011ቱ አብዮት በኋላ እየፈረሰች ባለበት ወቅት፣ አልጀዚራ ይፋ ባደረገው ሚስጥራዊ ሰነድ መሰረት፣ ካርቱም እና ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሙሌትና አሰራር በተመለከተ የቴክኒክ ስምምነት ተፈራርመዋል።
በሱዳን ድንበር ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ግድቡ በመጨረሻ እንደሚጠናቀቅና ሱዳንም ለራሷ ግድቦች የውሃ ፍሰትን ለመቆጣጠርና የኤሌክትሪክ አቅርቦቷን ለማረጋገጥ ከአዲስ አበባ ጋር አብሮ መስራት እንዳለባት በስውር አምናለች።
ይህ ጥገኝነት ዛሬ ይበልጥ ጎልቶ ይታያል። ካይሮ የሱዳንን ጦር ኃይሎች እየደገፈች ባለበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ ለሱዳን የኃይል አቅርቦት እየሰጠች ነው፣ ይህም ለሶስት አመታት ያልተከፈለ እና ከ90 ሚሊዮን ዶላር በላይ የደረሰ ዕዳ እየተጠራቀመ ነው። በዚህም ምክንያት ሱዳን በንግግር ደረጃ ግብጽ የምትደግፍ ስትሆን በተግባር ግን በኢትዮጵያ ላይ ጥገኛ ሆናለች። የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ግንባር በመበተኑ ምክንያት ግብጽ አሁን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ብቸኛ ሆናለች።
በተጨማሪም የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ሌላው ወሳኝ ለውጥ አሳይተዋል። በአሜሪካ እና በአለም ባንክ የሚመራው ድርድር ከከሸፈ በኋላ እንደ ዋና አስታራቂ ስትታይ የነበረችው የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አሁን ባለድርሻ ሆናለች። በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ከሆኑት ከሼክ ታህኖን ቢን ዛይድ ጋር ግንኙነት ያለው አንድ ድርጅት በቅርቡ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር የተፈራረመው የኃይል ግዢ ስምምነት አቡ ዳቢ አዲሱን ነባራዊ ሁኔታ መቀበል ብቻ ሳይሆን በንቃት እየተጠቀመችበት እንደሆነ ግልጽ ማሳያ ነው።
ግብፅ ከቀድሞ አጋሮቿ ወይም አሸማጋዮዎች ጋር መተማመን ስላልቻለች አዲስ ጥምረት ለመፍጠር ተገድዳለች። ለዚህም አጋጣሚውን የፈጠረው የኢትዮጵያ በ2024 ከሶማሊላንድ ጋር ያደረገችው የባህር በር ስምምነት ነው። ይህ ስምምነት የፌደራል መንግስቱን ያስቆጣና ያለፈቃድ የተደረገ በመሆኑ ግብጽ ይህን እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር ከሞቃዲሾ ጋር የደህንነት ስምምነት በፍጥነት በመፈረም፣ አዲሱን የኤርትራ-ግብጽ-ሶማሊያ የይዞታ ዘንግን መሰረተች።
ለኢትዮጵያ አወዛጋቢ የባህር በር ስምምነት ከሶማሊላንድ ጋር በምላሽ፣ የሶስቱ ሀገራት ጥምረት ለየአባላቱ ግልጽ ጥቅሞችን አስገኝቷል፡- ግብፅ በኢትዮጵያ ምስራቃዊ ድንበር ላይ ስትራቴጂካዊ ቦታ አገኘች፣ በራሷ ተነጥላ የነበረችው ኤርትራ በአብይ የአሰብ ወደብ ከተማን በተመለከተ ካላት ጠበኛ እቅድ ጋር ጠንካራ አጋር አገኘች፤ ሶማሊያ ደግሞ ከአል-ሻባብ ጋር በሚደረገው ውጊያ ተጨማሪ ድጋፍ እና ግዛቷ እንዳይከፋፈል የፀጥታ ዋስትና አገኘች ሲል ፊደል ፖስት ገልጿል።
9 months ago
በአባይ ወንዝ ላይ የተደረገው የውሃ "ጦርነት" አብቅቷል።ኢትዮጵያ አሸንፋለች ። የግብፅ እጅ ከታሰረ የሱዳንም ተሰብሯል።
ሱዳናዊው ፀሀፊ አልፋድል ኢብራሂም ህዳሴ ግድብን አስመልክቶ በአረብ ዊክሊ ላይ ከፃፈው ፅሁፍ የተወሰደ።
ፀሀፊው ህዳሴ ግድብ ላይ ግብፅ እንደተሸነፈች ቢገልፅም የኢትዮጵያን ወደብ መፈለግ በአዎንታዊ መልኩ መሳል አልፈለገም።
ለማንኛውም ፅሁፉ ይሄን ይመስላል;
ለ10 ዓመታት ያህል በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ትልቁ የውሃ ግጭት ሊሆን ይችላል ተብሎ የብዙዎች የትኩረት ስቦ ነበር። ታሪኩ ቀጥተኛ እና ሀይለኛ ነበር፡ ኢትዮጵያ እያደገች ያለችው የላይኛው ተፋሰስ ሀይል ግብጽን፣ ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የታችኛው ተፋሰስ የበላይ ተንሳፋፊ፣ የሚያንቀውን እና በመጨረሻም ጦርነት የሚያስነሳ ትልቅ ግድብ እየገነባች ነበር።
የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የ5 ቢሊዮን ዶላር ግድብን “በጥቁር ዘር ታሪክ ትልቁ ስኬት” ሲሉ አሞካሽተዋል፣ ትረካው ጷግሜ 4 ይፋዊ ፍጻሜውን አግኝቷል።
አንዴ በግብጽ እጅ የነበሩት የሥልጣን ጥንታዊ ማንሻዎች ዝገው ፈራርሰዋል። ዓለም አቀፍ ሽምግልና ጠፍቷል፣ የታችኛው ተፋሰስ ጥምረት ተበላሽቷል፣ እናም አዲስና ውስብስብ ጨዋታ አሁን በናይል ሸለቆ እየተካሄደ ነው—የዚህ ጨዋታ ሽልማቱ ራሱ ቦርዱ እንጂ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አይደለም።
የግብጽ ወታደራዊ አማራጭ ሙሉ በሙሉ መቋጨት በዚህ አዲስ እውነታ ውስጥ በጣም አስፈላጊው አካል ነው። ቀደም ሲል ዜናዎችን ሲቆጣጠር የነበረው የጦርነት ቅስቀሳ አሁን ባዶ ይመስላል። አንድ ሰው የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ2020 ግብጽ በመጨረሻ "ያንን ግድብ እንደምትደመሰስ" የሰጡትን ግልጽ ትንበያ ያስታውሳል። በወቅቱ አስተያየቱ በካይሮ ውስጥ እየታሰበበት የነበረውን አዋጭ፣ ምንም እንኳን ሥር ነቀል፣ የድርጊት አካሄድ ይወክል ነበር።
ያ አማራጭ አሁን ከፖለቲካዊ እና ወታደራዊ እይታ አንጻር ሊታሰብ የማይችል ነው። ግብፅ ሊፈቱ የሚገቡ ብዙ ጉዳዮች አሉባት። የእስራኤል ጥቃት በኳታር ላይ ከተሰነዘረ በኋላ ይበልጥ የካይሮ ችግር በሆነው በጋዛ ያለው አሰቃቂ ግጭት እና ከዚህም የመነጨው ሰብአዊ ጥፋት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የደህንነት ሀብቶቿን አሟጦታል።
ግብፅ ለጋዛ ወሳኝ አስታራቂ፣ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ሰዎች የስደተኞች መጠለያ እና ሰፊ ክልላዊ ሁከትን የምትከላከል እንደመሆኗ መጠን በደቡባዊ ድንበሯ ላይ ወታደራዊ ጀብዱ ለመፈጸም ፍላጎት የላትም። ካይሮ ከ125 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያን የመዋጋት አደጋን መውሰድ አትችልም ።
ይህ ስልታዊ ወደኋላ መመለስ የምስረታው ውጤት እና ሁኔታው ያመጣው ለውጥ ነው። የግብፅ ባለስልጣናት የኢትዮጵያን "አንድ ወገንተኝነት የተሞላበት እርምጃ" ማውገዝ እና ስለ "ህልውና አደጋ" አስከፊ ማስጠንቀቂያዎችን ማስተላለፋቸውን ሲቀጥሉ፣ የግብጽ ዕቅድ አውጪዎች ግን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሊቀበል የሚችል የወደፊት ሁኔታ በድብቅ እየፈጠሩ ነው። ለዚህም የግብጽ ከፍተኛ ጨዋማ ውሃ በማጥለል ንፁህ ውሃ ማቅረብ ኢንቨስትመንት ማረጋገጫ ሆኖ ያገለግላል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ማድቡሊ በቀጣዮቹ ስድስት ዓመታት በየቀኑ 10 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የተጣራ ውሃ ለማምረት ያለመውን ታላቅ እቅድ አስታውቀዋል። ከ100 በላይ የጨው ማስወገጃ ተቋማት ወደ ስራ የገቡ ሲሆን ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ሌሎችም ለመገንባት ታቅዷል። ግብፅ በናይል ወንዝ ላይ የነበራትን ጥገኝነት በመቀነስ የውሃ ደህንነቷን እንደ አዲስ እያሻሻለች ነው። አብዛኛውን የውሃ ድርሻ የሰጧት የ1929 እና 1959 ስምምነቶች ይደግፉት የነበረው የድሮው የውሃ ፖለቲካዊ ስርዓት ከጥቅም ውጪ መሆኑ በተዘዋዋሪ መንገድ ታውቋል። ካይሮ ግድቡን ከማፍረስ ይልቅ በግድቡ ዙሪያ እቅድ እያወጣች ነው።
ግብፅ እጇ ከታሰረች የሱዳን እጅም ተሰብሯል። ቀደም ሲል የግብጽ ዋና እና የውሃ ተጋሪ ሀገር የነበረችው ሱዳን ከፈረንጆቹ ከሚያዚያ 2023 ጀምሮ በአሰቃቂ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ገብታለች።
በአካባቢው የውክልና ግጭቶች መፋለሚያ በመሆኗ፣ የሀገሪቱ ዲፕሎማሲያዊ ተጽእኖ ቀንሷል። በዋና ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ደጋፊዋ በግብፅ ላይ የህልውና ጥገኛ በመሆኗ፣ በፖርት ሱዳን የሚገኘው በሱዳን ጦር ኃይሎች (ኤስ.ኤ.ኤፍ.) የሚመራው መንግስት በይፋ የካይሮን የፀረ-ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አቋም ለመደገፍ ተገድዷል።
ይሁን እንጂ፣ ያለው እውነታ እጅግ አሳዛኝ እና ውስብስብ ነው። በህዳር 2015፣ ከእርስ በርስ ጦርነቱ በፊት፣ ነገር ግን አገሪቷ ከ2011ቱ አብዮት በኋላ እየፈረሰች ባለበት ወቅት፣ አልጀዚራ ይፋ ባደረገው ሚስጥራዊ ሰነድ መሰረት፣ ካርቱም እና ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሙሌትና አሰራር በተመለከተ የቴክኒክ ስምምነት ተፈራርመዋል።
በሱዳን ድንበር ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ግድቡ በመጨረሻ እንደሚጠናቀቅና ሱዳንም ለራሷ ግድቦች የውሃ ፍሰትን ለመቆጣጠርና የኤሌክትሪክ አቅርቦቷን ለማረጋገጥ ከአዲስ አበባ ጋር አብሮ መስራት እንዳለባት በስውር አምናለች።
ይህ ጥገኝነት ዛሬ ይበልጥ ጎልቶ ይታያል። ካይሮ የሱዳንን ጦር ኃይሎች እየደገፈች ባለበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ ለሱዳን የኃይል አቅርቦት እየሰጠች ነው፣ ይህም ለሶስት አመታት ያልተከፈለ እና ከ90 ሚሊዮን ዶላር በላይ የደረሰ ዕዳ እየተጠራቀመ ነው። በዚህም ምክንያት ሱዳን በንግግር ደረጃ ግብጽ የምትደግፍ ስትሆን በተግባር ግን በኢትዮጵያ ላይ ጥገኛ ሆናለች። የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ግንባር በመበተኑ ምክንያት ግብጽ አሁን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ብቸኛ ሆናለች።
በተጨማሪም የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ሌላው ወሳኝ ለውጥ አሳይተዋል። በአሜሪካ እና በአለም ባንክ የሚመራው ድርድር ከከሸፈ በኋላ እንደ ዋና አስታራቂ ስትታይ የነበረችው የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አሁን ባለድርሻ ሆናለች። በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ከሆኑት ከሼክ ታህኖን ቢን ዛይድ ጋር ግንኙነት ያለው አንድ ድርጅት በቅርቡ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር የተፈራረመው የኃይል ግዢ ስምምነት አቡ ዳቢ አዲሱን ነባራዊ ሁኔታ መቀበል ብቻ ሳይሆን በንቃት እየተጠቀመችበት እንደሆነ ግልጽ ማሳያ ነው።
ግብፅ ከቀድሞ አጋሮቿ ወይም አሸማጋዮዎች ጋር መተማመን ስላልቻለች አዲስ ጥምረት ለመፍጠር ተገድዳለች። ለዚህም አጋጣሚውን የፈጠረው የኢትዮጵያ በ2024 ከሶማሊላንድ ጋር ያደረገችው የባህር በር ስምምነት ነው። ይህ ስምምነት የፌደራል መንግስቱን ያስቆጣና ያለፈቃድ የተደረገ በመሆኑ ግብጽ ይህን እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር ከሞቃዲሾ ጋር የደህንነት ስምምነት በፍጥነት በመፈረም፣ አዲሱን የኤርትራ-ግብጽ-ሶማሊያ የይዞታ ዘንግን መሰረተች።
ለኢትዮጵያ አወዛጋቢ የባህር በር ስምምነት ከሶማሊላንድ ጋር በምላሽ፣ የሶስቱ ሀገራት ጥምረት ለየአባላቱ ግልጽ ጥቅሞችን አስገኝቷል፡- ግብፅ በኢትዮጵያ ምስራቃዊ ድንበር ላይ ስትራቴጂካዊ ቦታ አገኘች፣ በራሷ ተነጥላ የነበረችው ኤርትራ በአብይ የአሰብ ወደብ ከተማን በተመለከተ ካላት ጠበኛ እቅድ ጋር ጠንካራ አጋር አገኘች፤ ሶማሊያ ደግሞ ከአል-ሻባብ ጋር በሚደረገው ውጊያ ተጨማሪ ድጋፍ እና ግዛቷ እንዳይከፋፈል የፀጥታ ዋስትና አገኘች።
ሱዳናዊው ፀሀፊ አልፋድል ኢብራሂም ህዳሴ ግድብን አስመልክቶ በአረብ ዊክሊ ላይ ከፃፈው ፅሁፍ የተወሰደ።
ፀሀፊው ህዳሴ ግድብ ላይ ግብፅ እንደተሸነፈች ቢገልፅም የኢትዮጵያን ወደብ መፈለግ በአዎንታዊ መልኩ መሳል አልፈለገም።
ለማንኛውም ፅሁፉ ይሄን ይመስላል;
ለ10 ዓመታት ያህል በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ትልቁ የውሃ ግጭት ሊሆን ይችላል ተብሎ የብዙዎች የትኩረት ስቦ ነበር። ታሪኩ ቀጥተኛ እና ሀይለኛ ነበር፡ ኢትዮጵያ እያደገች ያለችው የላይኛው ተፋሰስ ሀይል ግብጽን፣ ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የታችኛው ተፋሰስ የበላይ ተንሳፋፊ፣ የሚያንቀውን እና በመጨረሻም ጦርነት የሚያስነሳ ትልቅ ግድብ እየገነባች ነበር።
የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የ5 ቢሊዮን ዶላር ግድብን “በጥቁር ዘር ታሪክ ትልቁ ስኬት” ሲሉ አሞካሽተዋል፣ ትረካው ጷግሜ 4 ይፋዊ ፍጻሜውን አግኝቷል።
አንዴ በግብጽ እጅ የነበሩት የሥልጣን ጥንታዊ ማንሻዎች ዝገው ፈራርሰዋል። ዓለም አቀፍ ሽምግልና ጠፍቷል፣ የታችኛው ተፋሰስ ጥምረት ተበላሽቷል፣ እናም አዲስና ውስብስብ ጨዋታ አሁን በናይል ሸለቆ እየተካሄደ ነው—የዚህ ጨዋታ ሽልማቱ ራሱ ቦርዱ እንጂ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አይደለም።
የግብጽ ወታደራዊ አማራጭ ሙሉ በሙሉ መቋጨት በዚህ አዲስ እውነታ ውስጥ በጣም አስፈላጊው አካል ነው። ቀደም ሲል ዜናዎችን ሲቆጣጠር የነበረው የጦርነት ቅስቀሳ አሁን ባዶ ይመስላል። አንድ ሰው የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ2020 ግብጽ በመጨረሻ "ያንን ግድብ እንደምትደመሰስ" የሰጡትን ግልጽ ትንበያ ያስታውሳል። በወቅቱ አስተያየቱ በካይሮ ውስጥ እየታሰበበት የነበረውን አዋጭ፣ ምንም እንኳን ሥር ነቀል፣ የድርጊት አካሄድ ይወክል ነበር።
ያ አማራጭ አሁን ከፖለቲካዊ እና ወታደራዊ እይታ አንጻር ሊታሰብ የማይችል ነው። ግብፅ ሊፈቱ የሚገቡ ብዙ ጉዳዮች አሉባት። የእስራኤል ጥቃት በኳታር ላይ ከተሰነዘረ በኋላ ይበልጥ የካይሮ ችግር በሆነው በጋዛ ያለው አሰቃቂ ግጭት እና ከዚህም የመነጨው ሰብአዊ ጥፋት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የደህንነት ሀብቶቿን አሟጦታል።
ግብፅ ለጋዛ ወሳኝ አስታራቂ፣ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ሰዎች የስደተኞች መጠለያ እና ሰፊ ክልላዊ ሁከትን የምትከላከል እንደመሆኗ መጠን በደቡባዊ ድንበሯ ላይ ወታደራዊ ጀብዱ ለመፈጸም ፍላጎት የላትም። ካይሮ ከ125 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያን የመዋጋት አደጋን መውሰድ አትችልም ።
ይህ ስልታዊ ወደኋላ መመለስ የምስረታው ውጤት እና ሁኔታው ያመጣው ለውጥ ነው። የግብፅ ባለስልጣናት የኢትዮጵያን "አንድ ወገንተኝነት የተሞላበት እርምጃ" ማውገዝ እና ስለ "ህልውና አደጋ" አስከፊ ማስጠንቀቂያዎችን ማስተላለፋቸውን ሲቀጥሉ፣ የግብጽ ዕቅድ አውጪዎች ግን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሊቀበል የሚችል የወደፊት ሁኔታ በድብቅ እየፈጠሩ ነው። ለዚህም የግብጽ ከፍተኛ ጨዋማ ውሃ በማጥለል ንፁህ ውሃ ማቅረብ ኢንቨስትመንት ማረጋገጫ ሆኖ ያገለግላል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ማድቡሊ በቀጣዮቹ ስድስት ዓመታት በየቀኑ 10 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የተጣራ ውሃ ለማምረት ያለመውን ታላቅ እቅድ አስታውቀዋል። ከ100 በላይ የጨው ማስወገጃ ተቋማት ወደ ስራ የገቡ ሲሆን ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ሌሎችም ለመገንባት ታቅዷል። ግብፅ በናይል ወንዝ ላይ የነበራትን ጥገኝነት በመቀነስ የውሃ ደህንነቷን እንደ አዲስ እያሻሻለች ነው። አብዛኛውን የውሃ ድርሻ የሰጧት የ1929 እና 1959 ስምምነቶች ይደግፉት የነበረው የድሮው የውሃ ፖለቲካዊ ስርዓት ከጥቅም ውጪ መሆኑ በተዘዋዋሪ መንገድ ታውቋል። ካይሮ ግድቡን ከማፍረስ ይልቅ በግድቡ ዙሪያ እቅድ እያወጣች ነው።
ግብፅ እጇ ከታሰረች የሱዳን እጅም ተሰብሯል። ቀደም ሲል የግብጽ ዋና እና የውሃ ተጋሪ ሀገር የነበረችው ሱዳን ከፈረንጆቹ ከሚያዚያ 2023 ጀምሮ በአሰቃቂ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ገብታለች።
በአካባቢው የውክልና ግጭቶች መፋለሚያ በመሆኗ፣ የሀገሪቱ ዲፕሎማሲያዊ ተጽእኖ ቀንሷል። በዋና ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ደጋፊዋ በግብፅ ላይ የህልውና ጥገኛ በመሆኗ፣ በፖርት ሱዳን የሚገኘው በሱዳን ጦር ኃይሎች (ኤስ.ኤ.ኤፍ.) የሚመራው መንግስት በይፋ የካይሮን የፀረ-ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አቋም ለመደገፍ ተገድዷል።
ይሁን እንጂ፣ ያለው እውነታ እጅግ አሳዛኝ እና ውስብስብ ነው። በህዳር 2015፣ ከእርስ በርስ ጦርነቱ በፊት፣ ነገር ግን አገሪቷ ከ2011ቱ አብዮት በኋላ እየፈረሰች ባለበት ወቅት፣ አልጀዚራ ይፋ ባደረገው ሚስጥራዊ ሰነድ መሰረት፣ ካርቱም እና ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሙሌትና አሰራር በተመለከተ የቴክኒክ ስምምነት ተፈራርመዋል።
በሱዳን ድንበር ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ግድቡ በመጨረሻ እንደሚጠናቀቅና ሱዳንም ለራሷ ግድቦች የውሃ ፍሰትን ለመቆጣጠርና የኤሌክትሪክ አቅርቦቷን ለማረጋገጥ ከአዲስ አበባ ጋር አብሮ መስራት እንዳለባት በስውር አምናለች።
ይህ ጥገኝነት ዛሬ ይበልጥ ጎልቶ ይታያል። ካይሮ የሱዳንን ጦር ኃይሎች እየደገፈች ባለበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ ለሱዳን የኃይል አቅርቦት እየሰጠች ነው፣ ይህም ለሶስት አመታት ያልተከፈለ እና ከ90 ሚሊዮን ዶላር በላይ የደረሰ ዕዳ እየተጠራቀመ ነው። በዚህም ምክንያት ሱዳን በንግግር ደረጃ ግብጽ የምትደግፍ ስትሆን በተግባር ግን በኢትዮጵያ ላይ ጥገኛ ሆናለች። የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ግንባር በመበተኑ ምክንያት ግብጽ አሁን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ብቸኛ ሆናለች።
በተጨማሪም የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ሌላው ወሳኝ ለውጥ አሳይተዋል። በአሜሪካ እና በአለም ባንክ የሚመራው ድርድር ከከሸፈ በኋላ እንደ ዋና አስታራቂ ስትታይ የነበረችው የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አሁን ባለድርሻ ሆናለች። በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ከሆኑት ከሼክ ታህኖን ቢን ዛይድ ጋር ግንኙነት ያለው አንድ ድርጅት በቅርቡ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር የተፈራረመው የኃይል ግዢ ስምምነት አቡ ዳቢ አዲሱን ነባራዊ ሁኔታ መቀበል ብቻ ሳይሆን በንቃት እየተጠቀመችበት እንደሆነ ግልጽ ማሳያ ነው።
ግብፅ ከቀድሞ አጋሮቿ ወይም አሸማጋዮዎች ጋር መተማመን ስላልቻለች አዲስ ጥምረት ለመፍጠር ተገድዳለች። ለዚህም አጋጣሚውን የፈጠረው የኢትዮጵያ በ2024 ከሶማሊላንድ ጋር ያደረገችው የባህር በር ስምምነት ነው። ይህ ስምምነት የፌደራል መንግስቱን ያስቆጣና ያለፈቃድ የተደረገ በመሆኑ ግብጽ ይህን እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር ከሞቃዲሾ ጋር የደህንነት ስምምነት በፍጥነት በመፈረም፣ አዲሱን የኤርትራ-ግብጽ-ሶማሊያ የይዞታ ዘንግን መሰረተች።
ለኢትዮጵያ አወዛጋቢ የባህር በር ስምምነት ከሶማሊላንድ ጋር በምላሽ፣ የሶስቱ ሀገራት ጥምረት ለየአባላቱ ግልጽ ጥቅሞችን አስገኝቷል፡- ግብፅ በኢትዮጵያ ምስራቃዊ ድንበር ላይ ስትራቴጂካዊ ቦታ አገኘች፣ በራሷ ተነጥላ የነበረችው ኤርትራ በአብይ የአሰብ ወደብ ከተማን በተመለከተ ካላት ጠበኛ እቅድ ጋር ጠንካራ አጋር አገኘች፤ ሶማሊያ ደግሞ ከአል-ሻባብ ጋር በሚደረገው ውጊያ ተጨማሪ ድጋፍ እና ግዛቷ እንዳይከፋፈል የፀጥታ ዋስትና አገኘች።
9 months ago
“በሕይወት እያለሁ የግድቡን መጠናቀቅ የማየት ህልሜ እውን በመሆኑ ደስተኛ ነኝ”
- መሐመድ አልአሩሲ
#ethiooia | በሕይወት እያለሁ የግድቡን መጠናቀቅ የማየት ህልሜ እውን በመሆኑ ደስተኛ ነኝ ሲሉ መሐመድ አልአሩሲ ተናገሩ።
ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ጥብቅና በመቆም በአረብኛ ሲሟገቱ የሚታወቁት እና የምክር ቤት አባል የሆኑት ብሎም የውሀና ኢነርጂ ሚንስቴር አማካሪ መሐመድ አልአሩሲ ከኢፕድ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የዓባይ ግድብ ተጠናቆ ማየት ትልቁ ሕልማቸው እንደነበር ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለቅኝ ገዥዎች ያልተንበረከከች በተባበረ ክንድ አድዋ ላይ የጥቁሮች ኩራት የሆነውን ደማቅ ድል የተቀዳጀች ሀገር እንደመሆኗ መጠን ሕዳሴውንም አጠናቅቃ ሪቫን ለመቁረጥ በመዘጋጀቷ ደስተኛ ነኝ ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በቁጭት የጀመረችውን የሕዳሴ ግድብ በራሷ ፋይናንስ ምንጭነት ታሪክ በመስራቷ ዳግማዊ የዓድዋ ድል ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሐብቷ እንዳትጠቀም ብዙ ዘመቻዎች ሲደረጉ እንደነበር የገለፁት አቶ መሐመድ፤ በሁሉም መስክ ቁርጠኝነቷን በመሳየት የባንዳዎችን ምኞት ከንቱ ማድረግ እንደቻለች ጠቁመዋል።
የውጪና የውስጥ ጫናን በመቋቋም ግድቡን ለመመረቅ ጥቂት ቀናት የቀሯት ኢትዮጵያ ቀድሞውንም የሌሎች የዓባይ ተፋሰስ አገሮችን ጥቅም የመጉዳት ፍላጎት እንደሌላት በይፋ ስትገለፅ መቆየቷን አንስተዋል።
በዚሁ መሰረት የተፋሰሱ ሀገራት ብዥታ እንዲስተካከል የተጠናከረ የዲፕሎማሲ ስራ እንዲሁም በአረብኛ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ በመሟገትና ገለፃ በማድረግ ለምርቃት መብቃታችን ታላቅ ድል ነው ብለዋል።
የድል ብስራቱን ቀን ለማዬት ትልቅ ጉጉት ነበረኝ ያሉት አቶ መሐመድ፤ በሕይዎት እያለሁ በማየቴ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል ሲሉ ገልጸዋል።
ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሳይሰስቱ ግድቡ የእኔ ነው በማለት ያላቸውን አበርክተው የአንድነት አሻራቸውን አሳርፈው ደማቅ ድል ስላሰመዘገቡ ደስታቸው የላቀ መሆኑን በመግለጽ፤ በዚህም ኢትዮጵያ አሸንፋለች ሲሉ ገልጸዋል።
ይህን ደማቅ ድል በባሕር በርም መድገም ግድ ነው ያሉት አቶ መሐመድ፤ እሳቸውም በማንኛውም የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዳይ የማይደራደሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የፖለቲካ ልዩነት ሳይገድበን የአገራችንን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ የተለመደው አብሮነታችንን ማስቀጠል አለብን ሲሉ አሳስበዋል።
በዋስሁን ተክሌ #ኢትዮጵያ #ዓባይ #አባይ #ህዳሴ #ግድብ #ግብጽ #መሐመድ_አልአሩሲ
- መሐመድ አልአሩሲ
#ethiooia | በሕይወት እያለሁ የግድቡን መጠናቀቅ የማየት ህልሜ እውን በመሆኑ ደስተኛ ነኝ ሲሉ መሐመድ አልአሩሲ ተናገሩ።
ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ጥብቅና በመቆም በአረብኛ ሲሟገቱ የሚታወቁት እና የምክር ቤት አባል የሆኑት ብሎም የውሀና ኢነርጂ ሚንስቴር አማካሪ መሐመድ አልአሩሲ ከኢፕድ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የዓባይ ግድብ ተጠናቆ ማየት ትልቁ ሕልማቸው እንደነበር ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለቅኝ ገዥዎች ያልተንበረከከች በተባበረ ክንድ አድዋ ላይ የጥቁሮች ኩራት የሆነውን ደማቅ ድል የተቀዳጀች ሀገር እንደመሆኗ መጠን ሕዳሴውንም አጠናቅቃ ሪቫን ለመቁረጥ በመዘጋጀቷ ደስተኛ ነኝ ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በቁጭት የጀመረችውን የሕዳሴ ግድብ በራሷ ፋይናንስ ምንጭነት ታሪክ በመስራቷ ዳግማዊ የዓድዋ ድል ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሐብቷ እንዳትጠቀም ብዙ ዘመቻዎች ሲደረጉ እንደነበር የገለፁት አቶ መሐመድ፤ በሁሉም መስክ ቁርጠኝነቷን በመሳየት የባንዳዎችን ምኞት ከንቱ ማድረግ እንደቻለች ጠቁመዋል።
የውጪና የውስጥ ጫናን በመቋቋም ግድቡን ለመመረቅ ጥቂት ቀናት የቀሯት ኢትዮጵያ ቀድሞውንም የሌሎች የዓባይ ተፋሰስ አገሮችን ጥቅም የመጉዳት ፍላጎት እንደሌላት በይፋ ስትገለፅ መቆየቷን አንስተዋል።
በዚሁ መሰረት የተፋሰሱ ሀገራት ብዥታ እንዲስተካከል የተጠናከረ የዲፕሎማሲ ስራ እንዲሁም በአረብኛ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ በመሟገትና ገለፃ በማድረግ ለምርቃት መብቃታችን ታላቅ ድል ነው ብለዋል።
የድል ብስራቱን ቀን ለማዬት ትልቅ ጉጉት ነበረኝ ያሉት አቶ መሐመድ፤ በሕይዎት እያለሁ በማየቴ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል ሲሉ ገልጸዋል።
ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሳይሰስቱ ግድቡ የእኔ ነው በማለት ያላቸውን አበርክተው የአንድነት አሻራቸውን አሳርፈው ደማቅ ድል ስላሰመዘገቡ ደስታቸው የላቀ መሆኑን በመግለጽ፤ በዚህም ኢትዮጵያ አሸንፋለች ሲሉ ገልጸዋል።
ይህን ደማቅ ድል በባሕር በርም መድገም ግድ ነው ያሉት አቶ መሐመድ፤ እሳቸውም በማንኛውም የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዳይ የማይደራደሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የፖለቲካ ልዩነት ሳይገድበን የአገራችንን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ የተለመደው አብሮነታችንን ማስቀጠል አለብን ሲሉ አሳስበዋል።
በዋስሁን ተክሌ #ኢትዮጵያ #ዓባይ #አባይ #ህዳሴ #ግድብ #ግብጽ #መሐመድ_አልአሩሲ
9 months ago
“በሕይወት እያለሁ የግድቡን መጠናቀቅ የማየት ህልሜ እውን በመሆኑ ደስተኛ ነኝ”
- መሐመድ አልአሩሲ
በሕይወት እያለሁ የግድቡን መጠናቀቅ የማየት ህልሜ እውን በመሆኑ ደስተኛ ነኝ ሲሉ መሐመድ አልአሩሲ ተናገሩ።
ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ጥብቅና በመቆም በአረብኛ ሲሟገቱ የሚታወቁት እና የምክር ቤት አባል የሆኑት ብሎም የውሀና ኢነርጂ ሚንስቴር አማካሪ መሐመድ አልአሩሲ ከኢፕድ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የዓባይ ግድብ ተጠናቆ ማየት ትልቁ ሕልማቸው እንደነበር ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለቅኝ ገዥዎች ያልተንበረከከች በተባበረ ክንድ አድዋ ላይ የጥቁሮች ኩራት የሆነውን ደማቅ ድል የተቀዳጀች ሀገር እንደመሆኗ መጠን ሕዳሴውንም አጠናቅቃ ሪቫን ለመቁረጥ በመዘጋጀቷ ደስተኛ ነኝ ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በቁጭት የጀመረችውን የሕዳሴ ግድብ በራሷ ፋይናንስ ምንጭነት ታሪክ በመስራቷ ዳግማዊ የዓድዋ ድል ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሐብቷ እንዳትጠቀም ብዙ ዘመቻዎች ሲደረጉ እንደነበር የገለፁት አቶ መሐመድ፤ በሁሉም መስክ ቁርጠኝነቷን በመሳየት የባንዳዎችን ምኞት ከንቱ ማድረግ እንደቻለች ጠቁመዋል።
የውጪና የውስጥ ጫናን በመቋቋም ግድቡን ለመመረቅ ጥቂት ቀናት የቀሯት ኢትዮጵያ ቀድሞውንም የሌሎች የዓባይ ተፋሰስ አገሮችን ጥቅም የመጉዳት ፍላጎት እንደሌላት በይፋ ስትገለፅ መቆየቷን አንስተዋል።
በዚሁ መሰረት የተፋሰሱ ሀገራት ብዥታ እንዲስተካከል የተጠናከረ የዲፕሎማሲ ስራ እንዲሁም በአረብኛ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ በመሟገትና ገለፃ በማድረግ ለምርቃት መብቃታችን ታላቅ ድል ነው ብለዋል።
የድል ብስራቱን ቀን ለማዬት ትልቅ ጉጉት ነበረኝ ያሉት አቶ መሐመድ፤ በሕይዎት እያለሁ በማየቴ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል ሲሉ ገልጸዋል።
ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሳይሰስቱ ግድቡ የእኔ ነው በማለት ያላቸውን አበርክተው የአንድነት አሻራቸውን አሳርፈው ደማቅ ድል ስላሰመዘገቡ ደስታቸው የላቀ መሆኑን በመግለጽ፤ በዚህም ኢትዮጵያ አሸንፋለች ሲሉ ገልጸዋል።
ይህን ደማቅ ድል በባሕር በርም መድገም ግድ ነው ያሉት አቶ መሐመድ፤ እሳቸውም በማንኛውም የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዳይ የማይደራደሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የፖለቲካ ልዩነት ሳይገድበን የአገራችንን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ የተለመደው አብሮነታችንን ማስቀጠል አለብን ሲሉ አሳስበዋል።
በዋስሁን ተክሌ
- መሐመድ አልአሩሲ
በሕይወት እያለሁ የግድቡን መጠናቀቅ የማየት ህልሜ እውን በመሆኑ ደስተኛ ነኝ ሲሉ መሐመድ አልአሩሲ ተናገሩ።
ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ጥብቅና በመቆም በአረብኛ ሲሟገቱ የሚታወቁት እና የምክር ቤት አባል የሆኑት ብሎም የውሀና ኢነርጂ ሚንስቴር አማካሪ መሐመድ አልአሩሲ ከኢፕድ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የዓባይ ግድብ ተጠናቆ ማየት ትልቁ ሕልማቸው እንደነበር ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለቅኝ ገዥዎች ያልተንበረከከች በተባበረ ክንድ አድዋ ላይ የጥቁሮች ኩራት የሆነውን ደማቅ ድል የተቀዳጀች ሀገር እንደመሆኗ መጠን ሕዳሴውንም አጠናቅቃ ሪቫን ለመቁረጥ በመዘጋጀቷ ደስተኛ ነኝ ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በቁጭት የጀመረችውን የሕዳሴ ግድብ በራሷ ፋይናንስ ምንጭነት ታሪክ በመስራቷ ዳግማዊ የዓድዋ ድል ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሐብቷ እንዳትጠቀም ብዙ ዘመቻዎች ሲደረጉ እንደነበር የገለፁት አቶ መሐመድ፤ በሁሉም መስክ ቁርጠኝነቷን በመሳየት የባንዳዎችን ምኞት ከንቱ ማድረግ እንደቻለች ጠቁመዋል።
የውጪና የውስጥ ጫናን በመቋቋም ግድቡን ለመመረቅ ጥቂት ቀናት የቀሯት ኢትዮጵያ ቀድሞውንም የሌሎች የዓባይ ተፋሰስ አገሮችን ጥቅም የመጉዳት ፍላጎት እንደሌላት በይፋ ስትገለፅ መቆየቷን አንስተዋል።
በዚሁ መሰረት የተፋሰሱ ሀገራት ብዥታ እንዲስተካከል የተጠናከረ የዲፕሎማሲ ስራ እንዲሁም በአረብኛ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ በመሟገትና ገለፃ በማድረግ ለምርቃት መብቃታችን ታላቅ ድል ነው ብለዋል።
የድል ብስራቱን ቀን ለማዬት ትልቅ ጉጉት ነበረኝ ያሉት አቶ መሐመድ፤ በሕይዎት እያለሁ በማየቴ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል ሲሉ ገልጸዋል።
ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሳይሰስቱ ግድቡ የእኔ ነው በማለት ያላቸውን አበርክተው የአንድነት አሻራቸውን አሳርፈው ደማቅ ድል ስላሰመዘገቡ ደስታቸው የላቀ መሆኑን በመግለጽ፤ በዚህም ኢትዮጵያ አሸንፋለች ሲሉ ገልጸዋል።
ይህን ደማቅ ድል በባሕር በርም መድገም ግድ ነው ያሉት አቶ መሐመድ፤ እሳቸውም በማንኛውም የኢትዮጵያ ከፍታ ጉዳይ የማይደራደሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የፖለቲካ ልዩነት ሳይገድበን የአገራችንን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ የተለመደው አብሮነታችንን ማስቀጠል አለብን ሲሉ አሳስበዋል።
በዋስሁን ተክሌ
Sponsored by
Surafel