Logo
SeledaPost
ተሽሯል‼️
ከተቃውሞ በኋላ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ላይ ማሻሻያ ተደረገ።
በአገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ከፍተኛ ክርክር የፈጠረ የነበረው ድንጋጌ ከአዋጁ ማሻሻያ ረቂቅ እንዲወጣ ተደርጓል ፡፡

ይህ ድንጋጌ አገር በቀል ድርጅቶች ለፖለቲካዊ ቅስቀሳ (political advocacy) እና ከምርጫ ጋር ለተያያዙ ስራዎች ከውጭ የገንዘብ ምንጭ ገንዘብ እንዳይቀበሉ ይከለክል ነበር።

ቢቢሲ እንደዘገበው የማሻሻያ ረቂቁ አገር በቀል ድርጅቶች ከምርጫ ጋር የተያያዙ ማንኛውንም ስራ ለመስራት ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን "ቅድሚያ የድጋፍ ደብዳቤ ማግኘት" እንዳለባቸው ተቀምጧል።

በስራ ላይ ያለው አዋጅ ከስድስት ዓመት በፊት የጸደቀ ሲሆን፣ ቀደም ሲል የነበረውን እና "አፋኝ" በሚል የሚተቸውን አዋጅ ሙሉ ለሙሉ የሻረ ነበር። አዲሱ አዋጅ ለሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበት ነበር።

Seledadotio
Seledadotio
11 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.