መሬት በ31.5 ኢንች አዘነበለች ፤ የከርሰ-ምድር ውሃ መውጣት ዋነኛው መንስኤ ነው ተብሏል።
የሰው ልጅ ከመሬት በታች ያለውን የከርሰ-ምድር ውሃ ከመጠን በላይ በመምጠጡ ምክንያት፣ መሬት የምትሽከረከርበት ዘንግ በ31.5 ኢንች (በግምት 80 ሳንቲም ሜትር) ወደ ምስራቅ መዛመሙን ሳይንቲስቶች ገለጹ።
ፖፑላር መካኒክስ የተባለው የሳይንስ መጽሔት በዛሬው እትሙ (ሰኔ 4 ቀን 2026 እ.ኤ.አ) ይፋ እንዳደረገው፣ ከ1993 እስከ 2010 እ.ኤ.አ ባሉት ዓመታት ውስጥ ብቻ የሰው ልጅ ወደ 2,150 ጊጋቶን የሚጠጋ የከርሰ-ምድር ውሃ ለተለያዩ አገልግሎቶች አውጥቷል።
ይህ የወጣው ውሃ በመጨረሻ ወደ ውቅያኖሶች የፈሰሰ ሲሆን፣ በፕላኔቷ ላይ የነበረውን የክብደት ስርጭት ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል።
ተመራማሪዎች ሂደቱን ልክ አንድ የሚሽከረከር እሽክርክሪት ላይ በአንድ በኩል ትንሽ ክብደት ሲጨመርበት ሚዛኑን እንደሚስት አድርገውታል። ይህ ለውጥ በአየር ንብረት ላይ የሚያመጣው የረጅም ጊዜ ተጽዕኖ አሁንም ጥናት እየተደረገበት ሲሆን፣ የከርሰ-ምድር ውሃ መሟጠጥ ለባህር ወለል ከፍታ መጨመርም ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ተመልክቷል።
የሰው ልጅ ከመሬት በታች ያለውን የከርሰ-ምድር ውሃ ከመጠን በላይ በመምጠጡ ምክንያት፣ መሬት የምትሽከረከርበት ዘንግ በ31.5 ኢንች (በግምት 80 ሳንቲም ሜትር) ወደ ምስራቅ መዛመሙን ሳይንቲስቶች ገለጹ።
ፖፑላር መካኒክስ የተባለው የሳይንስ መጽሔት በዛሬው እትሙ (ሰኔ 4 ቀን 2026 እ.ኤ.አ) ይፋ እንዳደረገው፣ ከ1993 እስከ 2010 እ.ኤ.አ ባሉት ዓመታት ውስጥ ብቻ የሰው ልጅ ወደ 2,150 ጊጋቶን የሚጠጋ የከርሰ-ምድር ውሃ ለተለያዩ አገልግሎቶች አውጥቷል።
ይህ የወጣው ውሃ በመጨረሻ ወደ ውቅያኖሶች የፈሰሰ ሲሆን፣ በፕላኔቷ ላይ የነበረውን የክብደት ስርጭት ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል።
ተመራማሪዎች ሂደቱን ልክ አንድ የሚሽከረከር እሽክርክሪት ላይ በአንድ በኩል ትንሽ ክብደት ሲጨመርበት ሚዛኑን እንደሚስት አድርገውታል። ይህ ለውጥ በአየር ንብረት ላይ የሚያመጣው የረጅም ጊዜ ተጽዕኖ አሁንም ጥናት እየተደረገበት ሲሆን፣ የከርሰ-ምድር ውሃ መሟጠጥ ለባህር ወለል ከፍታ መጨመርም ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ተመልክቷል።
2 days ago