Logo
Zehabesha
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የአርሰናል ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ፣ ቡድናቸው የቻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታውን ካደረገ ማግስት በለንደን ጎዳናዎች ስለተዘጋጀው የዋንጫ የአደባባይ ዙረት (Parade) ተጠይቀው አጭር እና ቁርጠኝነት የተሞላበት ምላሽ ሰጥተዋል።

አሰልጣኙ በመጪው ሜይ 30 ከፓሪስ ሴንት ዠርመን (PSG) ጋር የሚያደርጉትን የቻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ በድል በማጠናቀቅ፣ አስቀድመው ካረጋገጡት የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ጋር አጣምረው ደስታቸውን ከደጋፊዎቻቸው ጋር ለማክበር ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ገልጸዋል። በመግለጫቸው ማጠቃለያ ላይም "የዋንጫ ዙረታችንን በሁለቱም ዋንጫዎች ታጅበን ማክበር እንፈልጋለን" በማለት ቡድናቸው አውሮፓን ለማንገስ እና ለታሪካዊው ድል ሙሉ በሙሉ የተዘጋጀ መሆኑን አረጋግጠዋል::

14 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.