Logo
Zehabesha
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ በሚያደርጉት ጦርነት ወቅት፣ የአሜሪካ የባህር ኃይል በኢራን ወደቦች ላይ የጣለውን የባህር ላይ እገዳ ሲያስፈጽም "እንደ የባህር ላይ ወንበዴዎች" (Pirates) እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ተናገሩ።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ይህንን አስተያየት የሰጡት፣ ከጥቂት ቀናት በፊት የአሜሪካ ኃይሎች አንድን መርከብ በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን በማብራራት ሜይ 1፣ 2026 በፍሎሪዳ ባደረጉት ንግግር ላይ ነው።

ትራምፕ በንግግራቸው፣ "መርከቧን ተቆጣጥረናል፣ ጭነቱን ወስደናል፣ ነዳጁንም ተቆጣጥረናል። ይህ በጣም አትራፊ የሆነ ስራ ነው፣" ካሉ በኋላ፤ "እኛ ልክ እንደ የባህር ላይ ወንበዴዎች ነን። በተወሰነ መልኩ የባህር ላይ ወንበዴዎችን እንመስላለን፣ ነገር ግን እኛ እየቀለድን አይደለም" ሲሉ ተደምጠዋል።

ከኢራን ወደቦች የተነሱ አንዳንድ የቴህራን መርከቦች፣ እንዲሁም ማዕቀብ የተጣለባቸው የኮንቴይነር ጫኝ መርከቦች እና በእስያ የውሀ ክልል ላይ የሚገኙ የኢራን የነዳጅ መርከቦች በአሜሪካ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሮይተርስ ዘገባ አክሎ አስታውሷል።

1 month ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.