እስራኤል፤ አሜሪካ የሆርሙዝ ወሽመጥን መዝጋቷን እንደምትደግፍ አስታወቀች
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔትያናሁ አሜሪካ ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረጉ የባሕር ጉዞዎችን ማገዷን እንደሚደግፉ ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለካቢኔያቸው በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት፤ “ፕሬዝዳንት ትራምፕ የባሕር ጉዟቸው ላይ እገዳ ለመጣል ወስነዋል። በእርግጥም ይህንን ጠንካራ አቋም እንደግፋለን” ብለዋል።
አሜሪካ እና ኢራን ፓኪስታን ውስጥ ካደረጉት ውጤት አልባው ንግግር በኋላ እሁድ ዕለት ከምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ጋር መነጋገራቸውንም ገልጸዋል።
ቫንስ “ዋነኛው ጉዳይ ሁሉንም የበለጸጉ [የኒውክሌር] ቁሶች ማስወገድ እና ምንም ተጨማሪ የማበልጸግ ተግባር እንደማይኖር ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነበር” ሲሉ እንደነገሯቸው በኔትያናሁ በቪዲዮ መልዕክታቸው አንስተዋል።
እንደ ኔትያናሁ ገለጻ የአሜሪካው ምክትል ፕሬዝዳንት ከፓኪስታ የተመለሱበት አውሮፕላን ውስጥ ሆነው የደወሉላቸው ሲሆን ከኢራን ጋር የሚደረገው ንግግር ደረሰበትን ደረጃ በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፤ አሜሪካ እና እስራኤል ያላቸው ግንኙነት በመካከላቸው መራራቅ እንዳለ ከሚጠቁሙ አስተያየቶች “ፍጹም ተቃራኒ” እንደሆነ ተናግረዋል።
BBC
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔትያናሁ አሜሪካ ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረጉ የባሕር ጉዞዎችን ማገዷን እንደሚደግፉ ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለካቢኔያቸው በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት፤ “ፕሬዝዳንት ትራምፕ የባሕር ጉዟቸው ላይ እገዳ ለመጣል ወስነዋል። በእርግጥም ይህንን ጠንካራ አቋም እንደግፋለን” ብለዋል።
አሜሪካ እና ኢራን ፓኪስታን ውስጥ ካደረጉት ውጤት አልባው ንግግር በኋላ እሁድ ዕለት ከምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ጋር መነጋገራቸውንም ገልጸዋል።
ቫንስ “ዋነኛው ጉዳይ ሁሉንም የበለጸጉ [የኒውክሌር] ቁሶች ማስወገድ እና ምንም ተጨማሪ የማበልጸግ ተግባር እንደማይኖር ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነበር” ሲሉ እንደነገሯቸው በኔትያናሁ በቪዲዮ መልዕክታቸው አንስተዋል።
እንደ ኔትያናሁ ገለጻ የአሜሪካው ምክትል ፕሬዝዳንት ከፓኪስታ የተመለሱበት አውሮፕላን ውስጥ ሆነው የደወሉላቸው ሲሆን ከኢራን ጋር የሚደረገው ንግግር ደረሰበትን ደረጃ በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፤ አሜሪካ እና እስራኤል ያላቸው ግንኙነት በመካከላቸው መራራቅ እንዳለ ከሚጠቁሙ አስተያየቶች “ፍጹም ተቃራኒ” እንደሆነ ተናግረዋል።
BBC
2 months ago