Logo
FIDEL POST NEWS
የሆርሙዝ ቀረጥ፦ ኢራን መርከቦችን በማሳለፍ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር እየሰበሰበች ነው

​ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ በሚያልፉ መርከቦች ላይ አዲስ የገንዘብ ክፍያ መጣሏ ተሰማ።

እንደ ሎይድስ ሊስት ዘገባ፣ "ደህንነቱ የተጠበቀ ኮሪደር" ለመጠቀም አንድ የነዳጅ መርከብ ኦፕሬተር 2 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ከፍሏል።

እስካሁን ዘጠኝ መርከቦች በዚህ ስልት ማለፋቸው የተረጋገጠ ሲሆን፣ ክፍያው ለአሜሪካና ለእስራኤል ግንኙነት የሌላቸውን መርከቦች ብቻ የሚመለከት ነው።

​የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ኃይል በላራክ ደሴት አቅራቢያ የመርከቦችን ማንነት በማረጋገጥ ፈቃድ ይሰጣል።

በሌላ በኩል፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኔቶ አጋሮች የኢራንን ጉዳይ በራሳቸው እንዲወጡት ማሳሰባቸው ከፍተኛ ቅሬታ ፈጥሯል።

የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በቀጠናው አዲስ የጉዞ ደንብ እንደሚዘረጋ በይፋ አስታውቀዋል።

​ምንጭ፦ ሎይድስ ሊስት
3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.