Logo
FIDEL POST NEWS
ተከዳው በማለት በምስራቅ ሐረርጌ መንታ ልጆቿ የገደለችው ኡርጂ መሐመድ በ23 ዓመት እስራት ተቀጣች

​"ባደረገችው ነገር አልተቆጨችም፤ ይልቁንም 'አባት የሌላቸውን ልጆች ማሳደግ ከባድ ስለሆነ ነው የገደልኳቸው' ስትል ለፖሊስ ቃሏን ሰጥታለች።"

በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ​በማያ ከተማ አስተዳደር አወዳይ ክፍለ ከተማ ጫልቱ ቀበሌ ውስጥ የተፈጸመው ይሄው አሰቃቂ ድርጊት፣ መላውን ነዋሪ አስደንግጧል። ጉዳዩ እንዲህ ነው፦

​የክህደቱ መጀመሪያ፦ ወጣት ኡርጂ በፍቅር ግንኙነት ውስጥ እያለች መንታ ልጆችን ትጸንሳለች። ይሁን እንጂ አባትየው እርግዝናውን እንደሰማ ጥሏት ይሰወራል።

​አሰቃቂው እርምጃ፦ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ወንድና ሴት መንታ ልጆችን በሰላም ብትገላገልም፣ ከቤት እንደገባች ግን በጭካኔ አፍና በመግደል በጓሮዋ ቀብራቸዋለች።

​ሚስጥሩን ያጋለጠው ድንጋይ፦ ድርጊቱን የጠረጠረው ታናሽ ወንድሟ፣ በጓሮ የተቆለለ አፈርና በላዩ ላይ የተቀመጡ ሁለት ትላልቅ ድንጋዮችን ተመልክቶ ለሀገር ሽማግሌዎች ጥቆማ ይሰጣል።

​የህግ ውሳኔ፦ ፖሊስ ባደረገው ምርመራ አስከሬኖቹ የወጡ ሲሆን፣ የማያ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤትም በፈጸመችው ከባድ የሰው መግደል ወንጀል የ23 ዓመት ፅኑ እስራት በይኖባታል።
4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.