ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ 1628 ተማሪዎች አስመረቀ
ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ ከሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እውቅና ባገኘበት በአውሮፕላን ጥገና ቴክኒሽያንነት ተማሪዎችን ተቀብሎ በማሰልጠን በዛሬው እለት የመጀመሪያውን ባች ያስመረቀ ብቸኛ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሆኗል።
ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ በድህረ ምረቃ፣ በቅድመ ምረቃ፣ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና እና በሰርተፊኬት ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ለ12ኛ ዙር በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር አስመርቋል።
ኮሌጁ በቅርቡ ናሽናል ዩኒቨርስቲ የመሆን ዓላማ ሰንቆ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል ያሉት የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ሰብስቤ ተፈሪ፣ ከዚህ አዲስና ትልቅ ግብ ጋር በተያያዘ ኮሌጁ የስልጠና ዘርፎችን በማስፋት በጤናው ዘርፍ በቅድመ ምረቃ ደረጃ በነርሲንግና በፋርማሲ ስልጠና መስጠት መጀመሩን አክለው ገልፀዋል።
ከ11 ዓመት በፊት የተቋቋመው ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ የናሽናል ኢንቨስትመንት ግሩፕ አባል እና የናሽናል ኤርዌይስ እህት ኩባንያ ሲሆን በሃገራችን በአቪዬሽን፣ በሆቴልና ቱሪዝም እያደገ የመጣውን የሰለጠነ የሰው ሀይል ፍላጎት ከሟሟላት አኳያ ለዘርፉ እድገት የበኩሉን አስተዋፅኦ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ብስራት ሬድዮ ሰምቷል።
ኮሌጁ እውቅና ባገኘባቸው በድህረ ምረቃ፣ በቅድመ ምረቃ የመጀመሪያ ዲግሪ መርሃግብሮች፣ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና መርሃግብሮች እንዲሁም ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እና ከአለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማህበር (IATA) ባገኘው ፍቃድ በአውሮፕላን ጥገና ቴክኒሽያን፣ በበረራ መስተንግዶ ፣በትኬት በርቀት መርሃ ግብር በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ እንዲሁም በቢዝነስ ማኔጅመንት እና ማርኬቲንግ ማኔጅመንት ፕሮግራሞች ስልጠና ይሰጣል።
ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ ከአለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማህበር (IATA) እና ከዓለም ኮሜርሻል ሜኔጅመንት (ICM) ባገኘው እውቅና መሰረት በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸው ስልጠናዎች እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን፣ በሚሰጠው የስልጠና ጥራትም ከ IATA ICM የ2009፣ 2010 እና የ2011 ለ3 ተከታታይ አመታት የአፍሪካ ምርጡ የስልጠና ማዕከል የሚል ሽልማት ማግኘቱን ብስራት ሰምቷል።
ኮሌጁ ለ12ኛ ጊዜ በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም በኢንተርናሽናል ትሬድ እና ኢኮኖሚክስ እንዲሁም ሎጅስቲክስ እና ሰፕላይ ማኔጅመንት 130 ተማሪዎችን አስመርቋል። በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና በደረጃ 4 በአካውንቲንግና ፋይናንስ፣ ፍሮንት ኦፊስ፣ ሃርድዌርና ኔትወርክ ሰርቪስ፣ ማርኬቲንግና ሴልስ ማኔጅመንት እንዲሁም በነርሲንግ እና ፋርማሲ 1035 ተማሪዎችን አስመርቋል።
በሰርተፊኬት ስልጠና በኤርክራፍትና ሜንቴናንስ ቴክኒሻን፣ ኤርላይን ካቢን ክሪው፣ ፍላይት ኦፕሬሽን ኦፊሰር እና በቲኬቲንግና ሪዘርቬሽን ያሰለጠናቸው 370 ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን በአጠቃላይ 1628 ተማሪዎች አስመርቋል።
seledadotio
seledadotio
ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ ከሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እውቅና ባገኘበት በአውሮፕላን ጥገና ቴክኒሽያንነት ተማሪዎችን ተቀብሎ በማሰልጠን በዛሬው እለት የመጀመሪያውን ባች ያስመረቀ ብቸኛ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሆኗል።
ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ በድህረ ምረቃ፣ በቅድመ ምረቃ፣ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና እና በሰርተፊኬት ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ለ12ኛ ዙር በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር አስመርቋል።
ኮሌጁ በቅርቡ ናሽናል ዩኒቨርስቲ የመሆን ዓላማ ሰንቆ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል ያሉት የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ሰብስቤ ተፈሪ፣ ከዚህ አዲስና ትልቅ ግብ ጋር በተያያዘ ኮሌጁ የስልጠና ዘርፎችን በማስፋት በጤናው ዘርፍ በቅድመ ምረቃ ደረጃ በነርሲንግና በፋርማሲ ስልጠና መስጠት መጀመሩን አክለው ገልፀዋል።
ከ11 ዓመት በፊት የተቋቋመው ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ የናሽናል ኢንቨስትመንት ግሩፕ አባል እና የናሽናል ኤርዌይስ እህት ኩባንያ ሲሆን በሃገራችን በአቪዬሽን፣ በሆቴልና ቱሪዝም እያደገ የመጣውን የሰለጠነ የሰው ሀይል ፍላጎት ከሟሟላት አኳያ ለዘርፉ እድገት የበኩሉን አስተዋፅኦ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ብስራት ሬድዮ ሰምቷል።
ኮሌጁ እውቅና ባገኘባቸው በድህረ ምረቃ፣ በቅድመ ምረቃ የመጀመሪያ ዲግሪ መርሃግብሮች፣ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና መርሃግብሮች እንዲሁም ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እና ከአለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማህበር (IATA) ባገኘው ፍቃድ በአውሮፕላን ጥገና ቴክኒሽያን፣ በበረራ መስተንግዶ ፣በትኬት በርቀት መርሃ ግብር በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ እንዲሁም በቢዝነስ ማኔጅመንት እና ማርኬቲንግ ማኔጅመንት ፕሮግራሞች ስልጠና ይሰጣል።
ናሽናል አቪዬሽን ኮሌጅ ከአለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማህበር (IATA) እና ከዓለም ኮሜርሻል ሜኔጅመንት (ICM) ባገኘው እውቅና መሰረት በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸው ስልጠናዎች እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን፣ በሚሰጠው የስልጠና ጥራትም ከ IATA ICM የ2009፣ 2010 እና የ2011 ለ3 ተከታታይ አመታት የአፍሪካ ምርጡ የስልጠና ማዕከል የሚል ሽልማት ማግኘቱን ብስራት ሰምቷል።
ኮሌጁ ለ12ኛ ጊዜ በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም በኢንተርናሽናል ትሬድ እና ኢኮኖሚክስ እንዲሁም ሎጅስቲክስ እና ሰፕላይ ማኔጅመንት 130 ተማሪዎችን አስመርቋል። በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና በደረጃ 4 በአካውንቲንግና ፋይናንስ፣ ፍሮንት ኦፊስ፣ ሃርድዌርና ኔትወርክ ሰርቪስ፣ ማርኬቲንግና ሴልስ ማኔጅመንት እንዲሁም በነርሲንግ እና ፋርማሲ 1035 ተማሪዎችን አስመርቋል።
በሰርተፊኬት ስልጠና በኤርክራፍትና ሜንቴናንስ ቴክኒሻን፣ ኤርላይን ካቢን ክሪው፣ ፍላይት ኦፕሬሽን ኦፊሰር እና በቲኬቲንግና ሪዘርቬሽን ያሰለጠናቸው 370 ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን በአጠቃላይ 1628 ተማሪዎች አስመርቋል።
seledadotio
seledadotio
7 months ago