Logo
SeledaPost
🇸🇦 የሳዑዲ መንግሥት በሥር የሰደዱ በሽታዎች የሚሰቃዩ ሰዎች ሐጅ እንዳያደርጉ ማቀዱ ተሰማ

በዚህ ምክንያት የሳዑዲ ሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር ምዕመናንን የሚልኩ ሁሉም አገራት ተገቢ ባለሥልጣናት እያንዳንዱን ምዕመን ሙሉ የጤና ምርመራ እንዲያደርግ ጠይቋል።

ምዕመኑ በጤንነቱ ላይ ምንም ዓይነት ስጋት እንደሌለበት የተረጋገጠለት መሆን አለበት።

የሳዑዲ ሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር ከዚህ ጋር በተያያዘ ምዕመናንን ወደሚልኩ አገራት ደብዳቤ ልኳል። ደብዳቤው ምዕመኑ ሐጅ እንዳያደርግ የማይፈቀድባቸውን አካላዊ ሁኔታዎች ዝርዝር መረጃ ይዟል።

የሰውነቱ ዋና ዋና አካላት ማንኛቸውም ተግባራቸውን ማከናወን ካልቻሉ አንድ ምዕመን ሐጅ እንዲያደርግ አይፈቀድለትም።

እነዚህም፡ ዳያሊሲስ የሚያስፈልገው የኩላሊት በሽታ፣ ከባድ የልብ ሕመም፣ የማያቋርጥ ኦክሲጅን የሚያስፈልገው የሳንባ በሽታ እና ከባድ የጉበት ስክለሮሲስን ይጨምራሉ።

በተጨማሪም፣ ከባድ የነርቭ ወይም የአእምሮ ሕመሞች፣ የመርሳት በሽታ ያለባቸው አረጋውያን፣ እና በማንኛውም ደረጃ ያሉ ከፍተኛ አደጋ ያለባቸው የደረሱ ነፍሰጡሮች ሐጅ እንዲያደርጉ አይፈቀድም።

የሳዑዲ መንግሥት እንደ ሳንባ ነቀርሳ ፣ የደም መፍሰስ ትኩሳት እና ተላላፊ በሽታዎች ያለባቸውን እና የኬሞቴራፒ ሕክምና ወይም ሌላ የተጠናከረ የበሽታ መከላከያ ህክምና እየወሰዱ ያሉ የካንሰር በሽተኞችንም ሐጅ እንዲያደርጉ አይፈቅድም ተብሏል።

ሳዑዲ ዓረቢያ ምዕመናንን የሚልኩትን ባለሥልጣናት እያንዳንዱ ምዕመን ከጤና ስጋቶች ነፃ መሆኑን የሚያረጋግጥ የግዴታ ትክክለኛ የጤና ሰርተፊኬት በኑሱክ መሳር መድረክ ላይ እንዲሰጡ ጠይቃለች።

መድረሻ እና መነሻ ቦታዎች ላይ በሚደረገው ቁጥጥር ላይ ሙሉ ትብብር እንዲደረግ ጥሪ ያቀረበው ደብዳቤው፣ የቁጥጥር ቡድኑ በኑሱክ መሳር መድረክ በኩል የተሰጠውን የጤና ሰርተፊኬት ትክክለኛነት እና ተዓማኒነት እንደሚያረጋግጥ ገልጿል።

ከአንድ አገር የመጣ ምዕመን በተዘረዘሩት የጤና እክሎች ከተገኘ፣ የሳዑዲ ሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር በዚያች አገር ላይ የማስተካከያ እና ገዳቢ እርምጃዎችን ይወስዳልም ተብሏል።

የእምነት ጉዳዮች ሚኒስቴር ከምዝገባው መጀመር በፊት በሥር የሰደዱ በሽታዎች የሚሰቃዩ ሰዎችን ለሐጅ እንዳይመዘገቡ መጠየቁን አስታውቋል።

seledadotio
seledadotio
7 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.