ጤና ልክ እንደ ሰላም በጣም አስፈላጊ ነገር ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጤና ልክ እንደ ሰላም በጣም አስፈላጊ ነገር ነው አሉ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተገነባው የላፍቶ ሆስፒታል በዛሬው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በኢትዮጵያ የጤና ፖሊሲ ባለፉት 10 ዓመታት ስንጠቀምት የነበረው ፖሊሲ ቅድሚያ መከላከል ላይ ያተኮረ ነበር፡፡
በዚህም መከላከል እንደተጠበቀ ሆኖ ታመው ከመጡ ማከም የሚለው ሀሳብ ተካትቶበት ፖሊሲው መሻሻሉን አውስተዋል፡፡
ጤና ልክ እንደ ሰላም በጣም አስፈላጊ ነገር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ካላመመን አናውቀውም፤ ሲያመን ነው የምናውቀው ሲሉም አስረድተዋል፡፡
በሽታ ልክ እንደ ጦር ሰራዊት ውጊያ እንደሚፈልግ ጠቅሰው፥ ውጊያው ደግሞ ትጥቅ ይፈልጋል ትጥቁ ደግሞ ምግብ ነው ብለዋል፡፡
በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች የመመገቢያ ማዕከል የተገነባው ሰዎች መብላት እንዲችሉና ማዕድ ማጋራት ልማድ አንዲሆን ነው ሲሉም አብራርተዋል፡፡
ተማሪዎች ቢያንስ በቀን ሁለቴ መብላት እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው የሚቸገሩ ሰዎች ስላሉ ይህ ልምምድ መጠናከር አለበት ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ዜጎቿን መርዳትና መመገብ እስክትቸል ድረስ ዜጎች በትብብር ይህንን ችግር ማለፍ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት፡፡
ይህንን እያደረግን ስንሄድ የተሟላ ጤንነት ያለው ትውልድና ማህበረሰብ ይፈጠራል ብለዋል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጤና ልክ እንደ ሰላም በጣም አስፈላጊ ነገር ነው አሉ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተገነባው የላፍቶ ሆስፒታል በዛሬው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በኢትዮጵያ የጤና ፖሊሲ ባለፉት 10 ዓመታት ስንጠቀምት የነበረው ፖሊሲ ቅድሚያ መከላከል ላይ ያተኮረ ነበር፡፡
በዚህም መከላከል እንደተጠበቀ ሆኖ ታመው ከመጡ ማከም የሚለው ሀሳብ ተካትቶበት ፖሊሲው መሻሻሉን አውስተዋል፡፡
ጤና ልክ እንደ ሰላም በጣም አስፈላጊ ነገር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ካላመመን አናውቀውም፤ ሲያመን ነው የምናውቀው ሲሉም አስረድተዋል፡፡
በሽታ ልክ እንደ ጦር ሰራዊት ውጊያ እንደሚፈልግ ጠቅሰው፥ ውጊያው ደግሞ ትጥቅ ይፈልጋል ትጥቁ ደግሞ ምግብ ነው ብለዋል፡፡
በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች የመመገቢያ ማዕከል የተገነባው ሰዎች መብላት እንዲችሉና ማዕድ ማጋራት ልማድ አንዲሆን ነው ሲሉም አብራርተዋል፡፡
ተማሪዎች ቢያንስ በቀን ሁለቴ መብላት እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው የሚቸገሩ ሰዎች ስላሉ ይህ ልምምድ መጠናከር አለበት ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ዜጎቿን መርዳትና መመገብ እስክትቸል ድረስ ዜጎች በትብብር ይህንን ችግር ማለፍ ይኖርባቸዋል ነው ያሉት፡፡
ይህንን እያደረግን ስንሄድ የተሟላ ጤንነት ያለው ትውልድና ማህበረሰብ ይፈጠራል ብለዋል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
9 days ago